የአፍሪካ ሕብረት ኮሚሽን አሜሪካ በአፍሪካ ሀገራት ላይ የጣለችው የጉዞ እገዳ እንዳሳሰበው አስታወቀ
14:29 06.06.2025 (የተሻሻለ: 15:04 06.06.2025)
© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱየአፍሪካ ሕብረት ኮሚሽን አሜሪካ በአፍሪካ ሀገራት ላይ የጣለችው የጉዞ እገዳ እንዳሳሰበው አስታወቀ

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
የአፍሪካ ሕብረት ኮሚሽን አሜሪካ በአፍሪካ ሀገራት ላይ የጣለችው የጉዞ እገዳ እንዳሳሰበው አስታወቀ
ኮሚሽኑ በትናንትናው ዕለት ባወጣው መግለጫ አሜሪካ ሉዓላዊ መብቷን ሚዛናዊ፣ ማስረጃ ላይ ተመስርታ እና በአሜሪካ እና በአፍሪካ መካከል ያለውን የረጅም ጊዜ አጋርነት በሚያንፀባርቅ መልኩ እንድትተገብር አሳስቧል።
እርምጃው በሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነት፣ በትምህርት ልውውጥ፣ በንግድ ትስስር እና ለብዙ አሥርተ ዓመታት በጥንቃቄ ሲገነባ በቆየው ሰፊ የዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ላይ ሊያስከትል የሚችለው አሉታዊ ተጽዕኖም ያሳስበኛል ብሏል።
አክሎም የአሜሪካ አስተዳደር ምክክር የታከለበት አካሄድ እንዲከተል እና ከሚመለከታቸው ሀገራት ጋር ገንቢ ውይይት እንዲያደርግ ጠይቋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X