የአማራ ክልል ባለፉት አስር ወራት ከውጭ ይገቡ የነበሩ ማዕድናትን በሀገር ውስጥ በመተካት ከ113 ሚሊየን ዶላር በላይ ማዳኑ ተገለፀ
16:07 05.06.2025 (የተሻሻለ: 16:24 05.06.2025)
© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱየአማራ ክልል ባለፉት አስር ወራት ከውጭ ይገቡ የነበሩ ማዕድናትን በሀገር ውስጥ በመተካት ከ113 ሚሊየን ዶላር በላይ ማዳኑ ተገለፀ

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
የአማራ ክልል ባለፉት አስር ወራት ከውጭ ይገቡ የነበሩ ማዕድናትን በሀገር ውስጥ በመተካት ከ113 ሚሊየን ዶላር በላይ ማዳኑ ተገለፀ
ክልሉ ይሄን ስኬት እንዴት ሊያስመዘግብ ቻለ፦
አማራ ክልል 1.43 ሚሊየን ቶን የማዕድን ምርቶችን በሀገር ውስጥ አማራጮች መተካት ችሏል።
በዚህም ከላይ የተጠቀሰውን የገንዘብ መጠን ያዳነ ሲሆን የኢንዱስትሪ ማዕድናት ብቻ 52.7 ሚሊየን የአሜሪካ ዶላር ድርሻ አላቸው።
በተጨማሪም ክልሉ በገቢ ንግድ ላይ የነበረውን ጥገኝነት ከመቀነስ ባሻገር የወጪ ንግድ ገቢውን አሳድጓል።
በተመሳሳይ ወቅት 8 ሺህ 770 ኪሎ ግራም ማዕድናትን ወደ ውጭ በመላክ ከ9 ሚሊየን ዶላር በላይ ገቢ አግኝቷል።
ካለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፀር የ44.5% ጭማሪ አሳይቷል።
ወርቅ ከወጪ ንግድ ከተገኘው ገቢ 64.7% በመቶውን በመሸፈን ቀዳሚ ነው ሲል የሀገር ውስጥ ሚዲያ የክልሉን የኮሚኒኬሽን ቢሮ ጠቅሶ ዘግቧል።
በሰው ሰራሽ አስተውሎት የበለፀገ ምሥል
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X