የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ላቭሮቭ እና የሩሲያ ከፍተኛ ተደራዳሪ ሜዲንስኪ በኢስታንቡል ውይይቶች ዙሪያ ለፑቲን ካቀረቡት ሪፖርት የተገኙ ቁልፍ መግለጫዎች፡-

ሰብስክራይብ

የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ላቭሮቭ እና የሩሲያ ከፍተኛ ተደራዳሪ ሜዲንስኪ በኢስታንቡል ውይይቶች ዙሪያ ለፑቲን ካቀረቡት ሪፖርት የተገኙ ቁልፍ መግለጫዎች፡-

የሩሲያ ልዑካን ቡድን ቭላድሚር ሜዲንስኪ ያነሷቸው ጉዳዮች፦

▪ሞስኮ እና ኪዬቭ በግጭት አፈታት ዙሪያ ሰነድ ተለዋውጠዋል፤ "ኳሱ አሁን በዩክሬን ሜዳ ላይ ነው"፣

▪ኪዬቭ በውይይቱ ላይ አቋምን ደግማ ገልጻለች - በ30 ቀናት የተኩስ አቁም ስምምነት በመጀመር ለሁለቱ ሀገራት መሪዎች ግኑኝነት መዘጋጀት፣

▪የሰብዓዊ ጉዳይ "ከድርድሩ ጎን የተደረገ ነበር"፣

▪ሁለቱ ወገኖች በመጀመሪያ - የቆሰሉ፣ በጠና የታመሙ፣ ከ25 ዓመት በታች የሆኑ የጦር እስረኞች ልውውጥ ለማድረግ ተስማምተዋል፣

▪ሩሲያ ከዩክሬን ጋር የጦር እስረኞች ልውውጥ ከግንቦት 30-ሰኔ 2 ድረስ ለማካሄድ ዝግጁ ነች።

የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሰርጌ ላቭሮቭ፡-

ዘለንስኪ የሞቱ እና የቆሰሉ ሰዎችን ለመሰብሰብ የሩሲያን የሁለት-ሶስት ቀን ጦርነትን የማቆም ጥያቄ ባለመቀበሉ ስህተት ሰርቷል፣

▪የሩሲያ እና ዩክሬን ልዑካን ስብሰባ ጠቃሚ እና ፍሬያማ ነበር፤ የድርድር ሂደቱ እየሠራ ነው፣

▪ሁለቱም ዙር ቀጥተኛ የሩሲያ-ዩክሬን ውይይቶች ተጨባጭ ውጤቶችን አስገኝተዋል፣

▪ውይይቶችን ለማደናቀፍ ለታለሙ ቅስቀሳዎች አለመሸነፍ  አስፈላጊ ነገር ነው።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0