- Sputnik አፍሪካ, 1920
The Rising South
የዓለም አቀፍ የኃይል ሚዛን እየተቀየረ ባለበት በዚህ ወቅት - ኢትዮጵያን፣ አፍሪካን እና ሌሎችን የሚቀርጹ የፖለቲካ፣ የኢኮኖሚ እና የማህበራዊ ሃይሎች ወደምንመለከትበት ወደ “ራይዚንግ ሳዉዝ” እንኳን በደህና መጡ፡፡ ደቡባዊ አመለካከቶችን ወደ ዓለም አቀፋዊ ውይይት መድረክ ስናቀርብ የአሰላሳዮችን ፣ የመሪዎችን እና የለዉጥ ፈጣሪዎችን ሃሳብ ያድምጡ።

ያረጁ ትርክቶችን ልሳን መዝጋት: ደቡባዊ ዓለም መጪውን ጊዜ የሚቀርጽበት ሂደት

ያረጁ ትርክቶችን ልሳን መዝጋት: ደቡባዊ ዓለም መጪውን ጊዜ የሚቀረጽበት ሂደት
ሰብስክራይብ
በዚህ የራይዚንግ ሳውዝ ዝግጅት በደቡባዊው ትብብር ድርጅት /Organization of Southern Cooperation/ የቴክኖሎጂ ፈጠራ እና ዲጂታላይዜሽን ማበልጸግ ምክትል ዋና ጸኃፊ የሆኑት ሹመቴ ግዛው /ፒ.ኤች.ዲ/ የዓለም አቀፉ የኃይል ሚዛን ስለሚቀየርበት መንገድ ወሳኝ ነጥቦችን አጋርተዋል።
“የደቡባዊው ትብብር ድርጅት በታላቁ ደቡባዊ ዓለም ውስጥ የሚገኙ ሀገራትን እና ማኅበረሰቦችን አቅም ማጎልበት ላይ ያምናል። ለአብነት ያህል ባህላዊ እና ሀገር-በቀል ዕውቀቶቻቸውን በመውሰድ ዓለም-አቀፍ በሆኑ መድረኮች ላይ እንዲሰሙ ያደርጋል።" በማለት ተናግረዋል።
ምክትል ዋና ጸኃፊዉ አክለዉም የዓለም-አቀፉ የፋይናንስ ሥርዓት ሀገራትን ዕዳ ውስጥ የሚዘፍቅ ነው በማለት ተችተዋል። የብሪክስን እሴቶች በሚጋራ መልኩ ባለብዙ ዋልታ እና ባለብዙ ዘርፍ የሆነ አዲስ ሞዴል እንደሚያስፈልግም ጠቁመዋል።
የዓለምን ሥርዓት በመቀየር ሂደት ሚዲያ ወሳኝ ሚና ይጫወታል ሲሉ አስረድተዋል ፤

"ስፑትኒክ ሚዲያ እዚህ አፍሪካ-ኢትዮጵያ ውስጥ ቢሮውን በመክፈቱ እና ፍትህን፣ እኩልነትን፣ ሁሉን አካታችነትን እንዲሁም በራስ ፈጠራ ላይ መሠረትን ያደረገ ትርክት ሳይሆን መሬት ላይ ባለ ተጨባጭ እውነት ላይ ስለሚሠራ ያለኝን አድናቆት መግለጽ እፈልጋለሁ።" በማለት ገልጸዋል።

🎧 የመጪውን ዓለም ሥርዓት የሚያስቃኘውን ይህንን የራይዚንግ ሳውዝ ፕሮግራም ይከታተላሉ።
ፖድካስታችንን በሌሎች አማራጮች ያድምጡ AfripodsDeezerPocket CastsPodcast AddictSpotify
አዳዲስ ዜናዎች
0