ኢትዮጵያ ለ6 ወር የሚቆይ የአካባቢ ብክለትን የመከላከል ዘመቻ ልትጀምር ነው
14:55 04.06.2025 (የተሻሻለ: 15:04 04.06.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
ኢትዮጵያ ለ6 ወር የሚቆይ የአካባቢ ብክለትን የመከላከል ዘመቻ ልትጀምር ነው
ግንቦት 30 በሚጀመረው ንቅናቄ ከ15 ሚሊየን በላይ ሕዝብ ቀጥተኛ ተሳትፎ ያደርጋል ተብሎ እንደሚጠበቅ የኢትዮጵያ አካባቢ ጥበቃ ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር ለሊሴ ነሜ ገልፀዋል።
"ፅዱ ኢትዮጵያ" በሚል መሪ ቃል በሚካሄደው ዘመቻ የከተሞች የድምጽ ብክለትን፣ የፕላስቲክ ብክለትን፣ የአፈርና የውሃ ብክለትን እንዲሁም የአየር ብክለትን መከላከል የሚያስችሉ ሥራዎች ይከናወናሉ ብለዋል።
ንቅናቄው በሁሉም ክልሎችና ከተማ አስተዳደሮች ተግባራዊ ይደረጋል መባሉን የሀገር ውስጥ ሚዲያ ዘግቧል፡፡
በሰው ሰራሽ አስተውሎት የበለፀገ ምሥል
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X