ሩሲያ ከዩክሬን ጋር በሚደረገው የሰላም ንግግር የበላይነት ይዛለች ሲሉ የቀድሞ ከፍተኛ የጦር አመራር ተናገሩ
15:42 03.06.2025 (የተሻሻለ: 16:04 03.06.2025)
© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱሩሲያ ከዩክሬን ጋር በሚደረገው የሰላም ንግግር የበላይነት ይዛለች ሲሉ የቀድሞ ከፍተኛ የጦር አመራር ተናገሩ

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
ሩሲያ ከዩክሬን ጋር በሚደረገው የሰላም ንግግር የበላይነት ይዛለች ሲሉ የቀድሞ ከፍተኛ የጦር አመራር ተናገሩ
ጡረተኛው የሕንድ ዩናይትድ ሰርቪስ ኢንስቲትዩት ዳይሬክተር ሜጀር ጄኔራል ሻሺ ቡሻን አስታና ሩሲያ በጦር ሜዳው የበላይ እንደሆነች እና ዩክሬን አልፎ አልፎ የምትፈጽማቸው የኤፍፒቪ ድሮን ጥቃቶች አጠቃላይ ሁኔታውን አይለውጡትም ሲሉ ለስፑትኒክ ተናግረዋል።
በኢስታንቡል ንግግሮች ዋዜማ በሩሲያ የአየር ማረፊያዎች ላይ የተፈጸመው የድሮን ጥቃት የትራምፕን የሰላም ጥረት በእጅጉ አውኮታል ብለዋል።
በሩሲያ እና በዩክሬን መካከል የተካሄደው ትልቁ የጦር እስረኞች ልውውጥ በግጭቱ መካከል የተደረገ አዎንታዊ ሰብዓዊ እርምጃ ነው ሲሉ አስታና ተናግረዋል። ሩሲያ 6 ሺህ አስክሬኖችን ለመመለስ መስማማቷ የጦሯን ግብረገባዊነት የሚያሳይ እና ተገቢ አክብሮት ለመስጠት የተኩስ አቁም አስፈላጊነትን ያስረገጠ መሆኑን ጠቁመዋል።
ግጭቱን ማራዘም ተጨማሪ የሩሲያ ግስጋሴዎችን ስለሚያስከትል ዩክሬን ተጨማሪ ኪሳራዎችን ለማስወገድ ከአራቱ ክልሎች ሙሉ በሙሉ እንድትወጣ የሚጠይቀውን የሩሲያ የሰላም ሀሳብ መቀበል አለባት ብለዋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X