የዚምባብዌ መሪ ሳዲክ በፓርላማ አባላት እና ዜጎች መካከል ያለውን የአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ ክፍተት ለማጥበብ እንዲሠራ ጥሪ አቀረቡ

© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱየዚምባብዌ መሪ ሳዲክ በፓርላማ አባላት እና ዜጎች መካከል ያለውን የአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ ክፍተት ለማጥበብ እንዲሠራ ጥሪ አቀረቡ
የዚምባብዌ መሪ ሳዲክ በፓርላማ አባላት እና ዜጎች መካከል ያለውን የአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ ክፍተት ለማጥበብ እንዲሠራ ጥሪ አቀረቡ - Sputnik አፍሪካ, 1920, 03.06.2025
ሰብስክራይብ

የዚምባብዌ መሪ ሳዲክ በፓርላማ አባላት እና ዜጎች መካከል ያለውን የአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ ክፍተት ለማጥበብ እንዲሠራ ጥሪ አቀረቡ

ኤመርሰን ምናንጋግዋ በቪክቶሪያ ፏፏቴ በተካሄደው 57ኛው የየደቡብ አፍሪካ ልማት ማሕበረሰብ (ሳዲክ) የፓርላማ መድረክ መክፈቻ ላይ ባደረጉት ንግግር ሰው ሰራሽ አስተውሎት ሀብትን በአግባቡ ለመጠቀም የሚያስችሉ መሳሪያዎችን እንደሚያቀርብ ተናግረዋል።

ቴክኖሎጂው መደበኛ እና ቀጥተኛ ግንኙነትን እንደሚያመቻችና ይህም ማስረጃ ላይ የተመሠረተ ፖሊሲ ለማውጣት እንደሚያስችል ተናግረዋል።

የወቅቱ የሳዲክ ሊቀመንበር የዚምባብዌን የሰው ሰራሽ አስተውሎት ተነሳሽነቶች በማሳያነት አንስተዋል፦

በመንግሥት አስተዳደር የዲጂታል መፍትሄዎችን ማሳደግ፣

የዩኒቨርሲቲ የፈጠራ ማዕከላትን ማቋቋም፣

ዲጂታል እውቀትን እና ምርምርን ለማሳደግ የሚደረጉ ሽርክናዎችን መፍጠር ይገኙበታል።

በተለይም የዚምባብዌ የሳይበር እና የመረጃ ጥበቃ ሕግ እንደ ሰው ሰራሽ አስተውሎት ነክ ያሉ የመረጃ ደህንነትን ለመቆጣጠር አንድ እርምጃ እንደሆነ ጠቅሰዋል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0