በሞሮኮ በጎች መወረሳቸው ወዝግብ አስነሳ
11:53 03.06.2025 (የተሻሻለ: 12:14 03.06.2025)
© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
በሞሮኮ በጎች መወረሳቸው ወዝግብ አስነሳ
የሞሮኮ መንግሥት የአየር ንብረት እና የኢኮኖሚ ችግሮችን በመጥቀስ በሀገሪቱ የተለመደውን የበግ መስዋዕት አግዷል።
ውሳኔው በሐይማኖት ነፃነት እና የቆዩ ልማዶች ላይ እንደተቃጣ ጥቃት በመታየቱ ትችት ማስከተሉን የመገናኛ ብዙኃን ዘገባዎች አመልክተዋል።
▪ በካዛብላንካ ባለሥልጣናት እንስሳትን በመያዛቸው ቁጣንና ግራ መጋባትን አስከትሏል፡፡
▪ በደርብ ጋሌፍ አንዳንዶች በድብቅ እንስሳትን በመሸጥ ሕዝባዊ ተቃውሟቸውን ገልጸዋል፡፡
▪ የሕግ አስከባሪ አካላት በኢኮኖሚያዊ እውነታዎች እና በሐይማኖታዊ ልምዶች መካከል እራሳቸውን አጣብቂኝ ውስጥ አግኝተዋል፡፡
የእንስሳት ሀብት ጥበቃ ትክክለኛ ስጋት ቢሆንም ብዙዎች መንግሥት የወሰደውን ጥብቅ እርምጃ እና ባሕልን ከአካባቢያዊ ፍላጎቶች ጋር ማጣጣም የሚችሉ አማራጮች አለመኖራቸውን ተችተዋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X
© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱ

© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱ
