በሩሲያ የዩክሬን የሰላም ሰነድ ላይ የሰፈሩ ቁልፍ ነጥቦች፦

በሩሲያ የዩክሬን የሰላም ሰነድ ላይ የሰፈሩ ቁልፍ ነጥቦች፦
▪ ሁለት የተኩስ አቁም ስምምነት አማራጮች ቀርበዋል።
▪ የመጀመሪያው አማራጭ የዩክሬን ጦር በዶንዬትስክ ሕዝባዊ ሪፐብሊክ፣ በሉሃንስክ ሕዝባዊ ሪፐብሊክ፣ ዛፖሮዢያ እና ሄርሶን ክልሎች ከያዟቸው የሩሲያ ግዛቶች መውጣትን ያካትታል።
▪ ሁለተኛው አማራጭ የወታደሮች ስምሪትን ማስቆም፣ ምልመላ እና ለኪዬቭ የሚደረገውን የውጭ ወታደራዊ ዕርዳታ ማቆም፣ ወታደሮችን መበተን እና የሶስተኛ ሀገራት ወታደራዊ ተሳትፎን ማስቀረት የተመለከቱ አንቀጾችን ያካትታል።
▪ ሰነዱ የዩክሬን ገለልተኝነትን እና ወታደራዊ ጥምረቶችን ለመቀላቀል ያላትን ውጥን መተው እንዳለባት ይገልጻል።
▪ በዩክሬን የሌሎች ሀገራትን ወታደራዊ እንቅስቃሴ የሚከለክል አንቀጽ ተካቷል።
▪ ዩክሬን ከኒውክሌር ነጻ መሆን እንዳለባትና የዩክሬን ሠራዊት ሊኖረው ስለሚገባ የመጨረሻ ቁጥር ያስቀምጣል።
▪ በሩሲያ ላይ የተጣሉት የኢኮኖሚ ማዕቀቦችን ማንሳት።
▪ ክራይሚያ፣ ዶኔዬትስክ፣ ሉሃንስክ፣ ዛፖሮዥዬ እና ሄርሰን ክልሎች የሩሲያ ግዛቶች ስለመሆናቸው ዓለም አቀፍ እውቅና መስጠት።
▪ በወታደራዊ እርምጃ ከደርሰው ጉዳት ጋር በተያያዘ የሚነሱ ጥያቄዎችን በጋራ ስምምነት ማንሳት።
▪ የሩሲያኛ ተናጋሪ ሕዝብ መብቶችን እና ነጻነቶችን ማረጋገጥ፣ በዩክሬን ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን እንቅስቃሴዎች ላይ የተጣሉትን ገደቦች ማንሳት እና ናዚዝምን ውድቅ ማድረግ።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

