ደቡብ አፍሪካ የጋዛ ዕርዳታ ማከፋፈያ ጣቢያ ላይ የተፈጸመውን ግድያ በማውገዝ አፋጣኝ ዓለም አቀፋዊ እርምጃ እንዲወሰድ ጥሪ አቀረበች

© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱደቡብ አፍሪካ የጋዛ ዕርዳታ ማከፋፈያ ጣቢያ ላይ የተፈጸመውን ግድያ በማውገዝ አፋጣኝ ዓለም አቀፋዊ እርምጃ እንዲወሰድ ጥሪ አቀረበች
ደቡብ አፍሪካ የጋዛ ዕርዳታ ማከፋፈያ ጣቢያ ላይ የተፈጸመውን ግድያ በማውገዝ አፋጣኝ ዓለም አቀፋዊ እርምጃ እንዲወሰድ ጥሪ አቀረበች - Sputnik አፍሪካ, 1920, 02.06.2025
ሰብስክራይብ

ደቡብ አፍሪካ የጋዛ ዕርዳታ ማከፋፈያ ጣቢያ ላይ የተፈጸመውን ግድያ በማውገዝ አፋጣኝ ዓለም አቀፋዊ እርምጃ እንዲወሰድ ጥሪ አቀረበች

የእስራኤል ኃይሎች በጋዛ ራፋህ አካባቢ በሚገኝ የምግብ እርዳታ ማከፋፈያ ጣቢያ አቅራቢያ የምግብ ዕርዳታ ለማግኘት በመጡ ሲቪሎች ላይ ጥቃት ፈጽመው ቢያንስ 31 ፍልስጤማውያን እንደተገደሉ እና ከ150 በላይ የሚሆኑት ደግሞ መቁሰላቸውን የጋዛ ጤና ሚኒስቴር አስታውቋል፡፡

“ደቡብ አፍሪካ አስቸኳይ እና ገለልተኛ ዓለም አቀፍ ምርመራ እንዲደረግ የቀረበውን ዓለም አቀፍ ጥሪ ተቀላቅላለች። እስራኤል እንደ ወራሪ ኃይል በዓለም አቀፍ የሰብዓዊ ሕግ መሠረት ሲቪሎችን የመጠበቅ እና ዕርዳታ በሰላም መድረሱን የማረጋገጥ ሕጋዊ ኃላፊነት አለባት” ሲል የሀገሪቱ  የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ገልጿል።

ደቡብ አፍሪካ የተባበሩት መንግሥታት የፍልስጤም ስደተኞች መጠለያና ሥራዎች ኤጀንሲ መገፋቱን አስመልክቶ፤ ሁኔታው በዓለም አቀፍ ሕግ የተከለከለው “ረሃብን እንደ ጦር መሳሪያ” መጠቀም ሊቆጠር ይችላል ስትል አስጠንቅቃለች።

“ዛሬ በጋዛ የተከሰቱት ክስተቶች አሳዛኝ አጋጣሚ አይደሉም፤ ይልቁንም በጋዛ ሕዝብ ላይ እየደረሰ ያለው ተከታታይ የቦምብ ጥቃት፣ እገዳ፣ ወረራ እና የጋራ ቅጣት ቀጥተኛ ውጤቶች ናቸው” ሲል ሚኒስቴሩ ገልጿል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0