ዓለም አቀፍ የህፃናት ቀን፡ "የአፍሪካ ትምህርት ከቅኝ አገዛዝ ነፃ መውጣት አለበት" ሲሉ ፕሮፌሰሩ ተናገሩ

© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱዓለም አቀፍ የህፃናት ቀን፡ "የአፍሪካ ትምህርት ከቅኝ አገዛዝ ነፃ መውጣት አለበት" ሲሉ ፕሮፌሰሩ ተናገሩ
ዓለም አቀፍ የህፃናት ቀን፡ የአፍሪካ ትምህርት ከቅኝ አገዛዝ ነፃ መውጣት አለበት ሲሉ ፕሮፌሰሩ ተናገሩ - Sputnik አፍሪካ, 1920, 01.06.2025
ሰብስክራይብ

ዓለም አቀፍ የህፃናት ቀን፡ "የአፍሪካ ትምህርት ከቅኝ አገዛዝ ነፃ መውጣት አለበት" ሲሉ ፕሮፌሰሩ ተናገሩ

በቅኝ ግዛት ተጽዕኖ ሥር ያለው የአፍሪካ የትምህርት ሥርዓት ከሀገር በቀል ዕውቀት ይልቅ ለምዕራባውያን ሞዴሎች ቅድሚያ ስለሚሰጥ ማኅበረሰቦች ችግሮቻቸውን በራሳቸው መንገድ እንዳይፈቱ አድርጓቸዋል ሲሉ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የልዩ ፍላጎት እና አካታች ትምህርት ክፍል ዳይሬክተር ፕሮፌሰር አለማየሁ ተክለማርያም ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል።

አክለውም ቋንቋ ለመረዳት እና ችግር ለመፍታት ቁልፍ በመሆኑ ህፃናት በአፍ መፍቻ ቋንቋቸው መማር አለባቸው ብለዋል። እውነተኛ እውቀት የሚገኘው ከሀገር በቀል አስተሳሰብ እና ማኅበረሰብ ላይ በተመሠረተ ምርምር እንደሆነ የገለፁት ፕሮፌሰሩ፤ ይህም ወደ አካባቢያዊ ፈጠራ እና ቴክኖሎጂ ሊያመራ እንደሚችል አስረድተዋል።

"ኢትዮጵያ በወታደራዊ ኃይል በጭራሽ ቅኝ አልተገዛችም፤ ነገር ግን ባህላችን ቅኝ ተገዝቷል። ስለዚህ አስተሳሰባችንን ከቅኝ አገዛዝ ነፃ ማውጣት አለብን" ሲሉ ፕሮፌሰር ተክለማርያም ተናግረዋል።

ፕሮፌሰሩ በቲክቶክ፣ ዩቲዩብ እና የውጭ ሚዲያዎች የተተኩት የአፍሪካ ባሕሎች እና የቃል ወጎች መነቃቃት እንደሚያስፈልጋቸውም አጽንኦት ሰጥተዋል።

በሰው ሰራሽ አስተውሎት የበለፀገ ምሥል

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0