የአፍሪካ ሀገራት ከሩሲያ የሚገዙት እህል መጠን እንደሚጨምር ይጠበቃል ተባለ
11:14 31.05.2025 (የተሻሻለ: 11:34 31.05.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
የአፍሪካ ሀገራት ከሩሲያ የሚገዙት እህል መጠን እንደሚጨምር ይጠበቃል ተባለ
የአፍሪካ የእህል ፍጆታ ከአህጉሪቱ ምርት እየበለጠ በመምጣቱ ፍላጎቱን ለማሟላት ከሩሲያ ጋር ያላትን የእህል ንግድ ግንኙነት እየጨመረች ነው። እ.ኤ.አ በ2024 የአፍሪካ ሀገራት ወደ 71 ሚሊየን ቶን የሚጠጋ እህል ከውጭ ያስገቡ ሲሆን የሩሲያ ድርሻ እየጨመረ መጥቷል።
የምስራቅ አፍሪካ የእህል ምክር ቤት ዋና ዳይሬክተር ጌራልድ ማሲላ፤ በሩሲያ እህል ፎረም ላይ ባደረጉት ንግግር የረዥም ጊዜ ንግድ፣ የማዳበሪያ አቅርቦት፣ የቴክኖሎጂ ድጋፍ እና የወደብ ማዘመን ከሩሲያ ጋር ያለውን ትብብር የበለጠ ሊያጠናክር ይችላል ሲሉ አጽንኦት ሰጥተዋል።
በአሁኑ ወቅት የሩሲያ የስንዴ አቅርቦት አንድ ሶስተኛውን የአፍሪካ የእህል ገበያ የሚሸፍን ሲሆን ምርቱ ለ40 ሀገራት ይደርሳል። ኤክስፖርቱ በስድስት የግብርና ወቅቶች ውስጥ በሶስት እጥፍ ጨምሯል። በአልጄሪያ፣ በኬንያ እና በቱኒዚያ ከፍተኛ እድገት አሳይቷል።
የጥቁር ባህር ኮሪደር እና ስትራቴጂካዊ አጋርነቶች ወሳኙን የንግድ ትስስር የበለጠ ሊያጠናክሩት እንደሚችሉ ማሲላ ለሩሲያ ሚዲያ በሰጡት ቃለ መጠየቅ አክለዋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X