የአፍሪካ ሀገራት ከሩሲያ የሚገዙት እህል መጠን እንደሚጨምር ይጠበቃል ተባለ

© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱየአፍሪካ ሀገራት ከሩሲያ የሚገዙት እህል መጠን እንደሚጨምር ይጠበቃል ተባለ
የአፍሪካ ሀገራት ከሩሲያ የሚገዙት እህል መጠን እንደሚጨምር ይጠበቃል ተባለ - Sputnik አፍሪካ, 1920, 31.05.2025
ሰብስክራይብ

የአፍሪካ ሀገራት ከሩሲያ የሚገዙት እህል መጠን እንደሚጨምር ይጠበቃል ተባለ

የአፍሪካ የእህል ፍጆታ ከአህጉሪቱ ምርት እየበለጠ በመምጣቱ ፍላጎቱን ለማሟላት ከሩሲያ ጋር ያላትን የእህል ንግድ ግንኙነት እየጨመረች ነው። እ.ኤ.አ በ2024 የአፍሪካ ሀገራት ወደ 71 ሚሊየን ቶን የሚጠጋ እህል ከውጭ  ያስገቡ ሲሆን የሩሲያ ድርሻ እየጨመረ መጥቷል።

የምስራቅ አፍሪካ የእህል ምክር ቤት ዋና ዳይሬክተር ጌራልድ ማሲላ፤ በሩሲያ እህል ፎረም ላይ ባደረጉት ንግግር የረዥም ጊዜ ንግድ፣ የማዳበሪያ አቅርቦት፣ የቴክኖሎጂ ድጋፍ እና የወደብ ማዘመን ከሩሲያ ጋር ያለውን ትብብር የበለጠ ሊያጠናክር ይችላል ሲሉ አጽንኦት ሰጥተዋል።

በአሁኑ ወቅት የሩሲያ የስንዴ አቅርቦት አንድ ሶስተኛውን የአፍሪካ የእህል ገበያ የሚሸፍን ሲሆን ምርቱ ለ40 ሀገራት ይደርሳል። ኤክስፖርቱ በስድስት የግብርና ወቅቶች ውስጥ በሶስት እጥፍ ጨምሯል። በአልጄሪያ፣ በኬንያ እና በቱኒዚያ ከፍተኛ እድገት አሳይቷል።

የጥቁር ባህር ኮሪደር እና ስትራቴጂካዊ አጋርነቶች ወሳኙን የንግድ ትስስር የበለጠ ሊያጠናክሩት እንደሚችሉ ማሲላ ለሩሲያ ሚዲያ በሰጡት ቃለ መጠየቅ አክለዋል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0