አሜሪካ ቦይንግ ላይ የተከፈተው የወንጀል ክስ እንዲዘጋ ጠየቀች
19:29 30.05.2025 (የተሻሻለ: 20:04 30.05.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
አሜሪካ ቦይንግ ላይ የተከፈተው የወንጀል ክስ እንዲዘጋ ጠየቀች
የሀገሪቱ የፍትሕ ሚኒስቴር በኢትዮጵያ እና ኢንዶኔዥያ ለ346 ሞት ምክንያት ከሆነው የማክስ አውሮፕላን መከስከስ ጋር ተያይዞ በግዙፉ የአሜሪካ ኩባንያ ላይ የቀረበውን የማጭበርበር ወንጀል ክስ እንዲዘጋ ጠይቋል።
በትናንትናው ዕለት ቀርቧል የተባለው ይህ ጥያቄ የአውሮፕላን አምራቹ የፌደራል አቪየሽን ባለሥልጣናት የሚያካሄዱትን ምርመራ በማደናቀፍ ከቀረበበት ክስ ለማምለጥ ስምምነት ላይ መድረሱን ተከትሎ የመጣ ነው።
ቦይንግ ክሱን ለማዘጋት ለተጎጂ ቤተሰቦች የሚሰጠውን ተጨማሪ 445 ሚሊየን ዶላር ጨምሮ በአጠቃላይ ከ1.1 ቢልየን ዶላር በላይ ለመክፈል መስማማቱን የአሜሪካ ሚዲያዎች ዘግበዋል።
በአደጋው ሴት ልጃቸውን ያጡት ናዲያ ማሌሮን የአሜሪካ መንግሥት ስምምነቱ "እውነተኛ ተጠያቂነትን" ያመጣል በማለቱ ማዘናቸውን ገልፀው "በስምምነቱ ምክንያት ተጠያቂ አይኖርም" ብለዋል።
ቦይንግ ሰራሾቹ ማክስ 737 አውሮፕላኖች በጥቅምት 2011 ዓ.ም በኢንዶኔዥያ በተመሳሳይ አመት መጋቢት ወር አዲስ አበባ አቅራቢያ መከስከሳቸው የሚታወስ ነው።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X