- Sputnik አፍሪካ, 1920
The Rising South
የዓለም አቀፍ የኃይል ሚዛን እየተቀየረ ባለበት በዚህ ወቅት - ኢትዮጵያን፣ አፍሪካን እና ሌሎችን የሚቀርጹ የፖለቲካ፣ የኢኮኖሚ እና የማህበራዊ ሃይሎች ወደምንመለከትበት ወደ “ራይዚንግ ሳዉዝ” እንኳን በደህና መጡ፡፡ ደቡባዊ አመለካከቶችን ወደ ዓለም አቀፋዊ ውይይት መድረክ ስናቀርብ የአሰላሳዮችን ፣ የመሪዎችን እና የለዉጥ ፈጣሪዎችን ሃሳብ ያድምጡ።

ብዝኃ-ሕይወት እና ሉዓላዊነት:- ከተፈጥሮ ጋር ስምም ለመፍጠር ኢትዮጵያ የያዘችው መንገድ

ብዝኃ-ሕይወት እና ሉዓላዊነት:- ከተፈጥሮ ጋር ስምም ለመፍጠር ኢትዮጵያ የያዘችው መንገድ
ሰብስክራይብ
የኢትዮጵያ ብዝኃ-ሕይወት ተቋም የአመራር አካላት ከሆኑት ከዶ/ር አብዮት ብርሃኑ እና ከአቶ ውብሸት ተሾመ ጋር የዓለም-አቀፍ የብዝኃ-ሕይወት ቀንን አስመልክቶ ከራይዚንግ ሳውዝ ጋር የተደረገ ቆይታ!

አቶ ውብሸት "ከ83,000 በላይ ናሙናዎች በቀዝቃዛ ክፍል እንዲሁም ከ9,000 በላይ የሚሆኑ ዝርያዎች በመስክ የዘረ-መል ባንክ ውስጥ ተጠብቀዋል።" ብለዋል። አክለውም ከሩሲያ ጋር በዘረ-መል ልውውጥ፣ በእውቀት እና ቴክኖሎጂ ሽግግር የዳበረ ትብብር እንደሚፈጠርም ያላቸውን ተስፋ ተናግረዋል።

ዶ/ር አብዮት በበኩላቸው "የዘረ-መል ዝርፊያን የናጎያ ስምምነትን በመከተል እና የብዝኃ-ሕይወት ሀብትን ለመጠበቅ ሲባል እያደገ የመጣውን የአፍሪካ ሀገራት ትብብር በማጠናከር ለውጥ ማምጣት እንችላለን። በማለት አጽንኦት ሰጥተው ተናግረዋል።
ባለሙያዎቹ ከአጼ ኃይለሥላሴ ጋር በመሆን የኢትዮጵያን ብዝኃ-ሰብል የፈጠረውን ኒኮላይ ቫቪሎቭ የተባለውን ሩሲያዊ በማድነቅ በኢትዮጵያ እና በሩሲያ የብዝኃ-ሀብት ጥበቃ የጋራ ትስስር ታሪክ ውስጥ ሁልጊዜም ሲታወስ ይኖራል ብለዋል።
የኢትዮጵያን የተፈጥሮ ቅርስ ሀብት እና በዓለም-አቀፍ የብዝኃ-ሕይወት ወስጥ ያላትን የአመራር ሚና በጥልቀት ለመረዳት ይህን ፕሮግራም ይከታተሉ።

ፖድካስታችንን በሌሎች አማራጮች ያድምጡ AfripodsDeezerPocket CastsPodcast AddictSpotify
አዳዲስ ዜናዎች
0