ምዕራባውያን ወደ ዩክሬን የሚልኩት የጦር መሳሪያ በአፍሪካ ሽብርተኝነት እንዲባባስ ማድረጉን የሩሲያ ባለሥልጣን አስታወቁ
20:00 29.05.2025 (የተሻሻለ: 20:24 29.05.2025)
© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱምዕራባውያን ወደ ዩክሬን የሚልኩት የጦር መሳሪያ በአፍሪካ ሽብርተኝነት እንዲባባስ ማድረጉን የሩሲያ ባለሥልጣን አስታወቁ

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
ምዕራባውያን ወደ ዩክሬን የሚልኩት የጦር መሳሪያ በአፍሪካ ሽብርተኝነት እንዲባባስ ማድረጉን የሩሲያ ባለሥልጣን አስታወቁ
"የአፍሪካ አህጉር የደህንነት ሁኔታ አሳሳቢ ሆኖ ቀጥሏል" ሲሉ በሩሲያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የአፍሪካ ቢሮ ኃላፊ ታቲያና ዶቭጋሌንኮ በሞስኮ በተካሄደው 13ኛው የደህንነት ጉዳዮች ከፍተኛ ተወካዮች ዓለም አቀፍ ስብሰባ ላይ ተናግረዋል።
ሁኔታው አሳሳቢ የሆነው ለምንድን ነው?
▪ዩክሬን ሳህል ውስጥ የሚገኙ የሽብር ቡድኖችን በቀጥታ እያሰለጠነች ነው።
▪ታጣቂ ቡድኖች ዘመናዊ ቴክኖሎጂዎችን እና አዳዲስ የሽብር ዘዴዎችን በመጠቀም የፀረ-ሽብር ጥረቶችን እየተቋቋሙ ነው።
▪እ.ኤ.አ 2024 በአፍሪካ የተፈፀሙ የሽብር ጥቃቶች በዓለም አቀፍ ደረጃ ከሽብርተኝነት ጋር ተያይዞ ከተመዘገበው ሞት ከ60 ከመቶ በላይ ድርሻ ይዘዋል።
ሩሲያ ሽብርተኝነትን ለመዋጋት ምን እያደረገች ነው?
▫የአፍሪካ ሕብረት ሽብርተኝነትን፣ ወንጀልንና የአደንዛዥ ዕፅ ዝውውርን ለመዋጋት የሚያደርገውን ጥረት ትደግፋለች።
▫በሩሲያ ጦር አሰልጣኞች ወታደራዊ ስልጠና መስጠትን ጨምሮ ለአፍሪካ መረጋጋት ድጋፍ ማድረጓን ትቀጥላለች።
በሰው ሰራሽ አስተውሎት የበለፀገ ምሥል
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X