ኢትዮጵያ የትምህርት ጥራትን ለማሳደግ ሰው ሰራሽ አስተውሎትን በትምህርት ስርዓቱ ውስጥ ለማዋሃድ አቅዳለች
15:09 29.05.2025 (የተሻሻለ: 15:24 29.05.2025)
© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱኢትዮጵያ የትምህርት ጥራትን ለማሳደግ ሰው ሰራሽ አስተውሎትን በትምህርት ስርዓቱ ውስጥ ለማዋሃድ አቅዳለች

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
ኢትዮጵያ የትምህርት ጥራትን ለማሳደግ ሰው ሰራሽ አስተውሎትን በትምህርት ስርዓቱ ውስጥ ለማዋሃድ አቅዳለች
ቴክኖሎጂውን በዘላቂነት ለመተግበር የትምህርት ሚኒስቴር ለ34 ሺህ የከፍተኛ ትምህርት መምህራን ሰፊ ስልጠና በመስጠት ላይ ይገኛል።
በትምህርት ሚኒስቴር የኢንፎርሜሽን ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጂ ዋና ዳይሬክተር ዘላለም አሰፋ ተማሪዎችና አስተማሪዎች የሰው ሰራሽ አስተውሎት እውቀት ሊናራቸው ይገባል ብለዋል።
ቴክኖሎጂው ተማሪዎችን ለመከታተል፣ ኩረጃን ለማስቀረት እና በትምህርት ስርዓቱ ውስጥ ተዓማኒነትን ለማዳበር ሥራ ላይ እንደሚውል ለሀገር ውስጥ የቴሌቪዥን ጣቢያ ገልጸዋል።
እቅዱ ከአሪዞና ዩኒቨርስቲ ጋር በመተባበር የሚተገበር ነው ተብሏል።
በሰው ሰራሽ አስተውሎት የበለፀገ ምሥል
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X