⭐ በአዲስ አበባ 11 ሆቴሎች የባለ 5 ኮከብ ደረጃ ተሰጣቸው
13:04 29.05.2025 (የተሻሻለ: 13:24 29.05.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
⭐ በአዲስ አበባ 11 ሆቴሎች የባለ 5 ኮከብ ደረጃ ተሰጣቸው
የቱሪዝም ሚኒስቴር አዲስ አበባ በሚገኙ 92 ሆቴሎች ላይ ሲያደርግ የቆየውን የደረጃ ምደባ ውጤት ዛሬ ይፋ አድርጓል።
የምደባው ውጤት፦
በመዲናዋ ከተመዘኑ 92 ሆቴሎች ውስጥ 40 የሚሆኑት ብቻ በተለያየ እርከን የኮከብ ደረጃዎችን አግኝተዋል፡፡
በምዘናው መሠረት 11 ሆቴሎች ባለ 5 ኮከብ፣ 9 ሆቴሎች ባለ 4 ኮከብ፣ 7 ሆቴሎች ባለ 3 ኮከብ፣ 5 ሆቴሎች ባለ 2 ኮከብ እና 2 ሆቴሎች ባለ 1 ኮከብ ሆነው ተመድበዋል፡፡
ከ40ዎቹ ሆቴሎች ውስጥ 34 የሚሆኑት ዳግም ምደባ የተሰጣቸው ሲሆን 6 የሚሆኑት ለዘርፉ አዲስ ናቸው።
የኮከብ ምደባው ለቀጣዮቹ 3 ዓመታት ብቻ እንደሚያገለግል ተገልጿል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X