የጀርመን ፓርላማ አባል በታውረስ ሚሳኤል ዙሪያ ይፋ የሆነው የሕዝብ አስተያየት የጀርመንን ሕዝብ ፍላጎት አይገልፅም አሉ
18:46 28.05.2025 (የተሻሻለ: 19:04 28.05.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
የጀርመን ፓርላማ አባል በታውረስ ሚሳኤል ዙሪያ ይፋ የሆነው የሕዝብ አስተያየት የጀርመንን ሕዝብ ፍላጎት አይገልፅም አሉ
"እነዚህ ቁጥሮች [51% የሚሆኑ ጀርመኖች ታውረስ ሚሳኤሎችን ዩክሬን እንድታገኝ ይደግፋሉ፤ 49% ይቃወማሉ] በጀርመን ያለውን አስተያየት አይገልጹም ብዬ አምናለሁ" ሲሉ የኦልተርነቲቭ ፎር ጀርመኒ ፓርቲ የቡንደስታግ የሕግ አውጪ ስቴፈን ኮትሬ ለስፑትኒክ ተናግረዋል።
"በጀርመን የሚገኙ መገናኛ ብዙኃን አንድ ርዕስ ብቻ ነው ያላቸው - ዩክሬንን መደገፍ።"
"ገለልተኛ መገናኛ ብዙኃን ቢኖሩን ጦር መሳሪያ አቅርቦትን የሚደግፉ አናሳ ቁጥር ብቻ ነበር የምናገኘው!"
"አብዛኛዎቹ ጀርመኖች ታውረስ ሚሳኤሎችን [ወደ ዩክሬን] መላክ የሚያስከትለውን መዘዝ አይረዱም።"
"የቡንደስታግ ሳይንሳዊ አገልግሎትም እንኳ 'ከሁለት ዓመት በፊት መዘዙ ግልጽ አልነበረም' ሲል አምኗል።"
"ጀርመኖች አደጋዎቹን ቢያውቁ ኖሮ የሕዝብ አስተያየት መስጫዎች በጣም የተለየ መልክ ይኖራቸው ነበር" ብለዋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X