የቻይና ባሕል ተሳትፎ በኢትዮጵያ እያደገ መምጣቱ ተነገረ
16:11 27.05.2025 (የተሻሻለ: 16:34 27.05.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
የቻይና ባሕል ተሳትፎ በኢትዮጵያ እያደገ መምጣቱ ተነገረ
በአዲስ አበባ ተካሂዶ የነበረው 24ኛው "ቻይኒዝ ብሪጅ" የቋንቋ ውድድር ቻይናን ከዓለም ዓቀፉ ማሕብረሰብ ጋር ያገናኘ ነው ሲሉ በኢትዮጵያ የቻይና አምባሳደር ተናግረዋል።
"ተወዳዳሪዎቹ የቻይና ቋንቋ ብቃታቸውን እና የጥበብ ተሰጥኦቸውን ሲያሳዩ እና ለቻይና ባሕልና ሕዝብ ያላቸውን ጥልቅ ፍቅር ሲገልጹ ማየት በጣም ያስደስታል" ብለዋል አምባሳደር ቼን።
የኢትዮጵያ ቱሪዝም ሚኒስትር ደኤታ ሰለሺ ግርማ ዝግጅቱ በሁለቱ ሀገሮች መካከል እያደገ የመጣውን የባሕል ልውውጥ የሚያሳይ ነው በማለት አወድሰውታል ሲል ሺንዋ ዘግቧል።
"ቋንቋ መማር የመጀመሪያው እርምጃ እና ለእድገት ቁልፍ ነው። በኢትዮጵያ ተወዳዳሪዎች የቀረቡት የባሕል ትርዒቶች በኢትዮጵያና በቻይና መካከል እያደገ የመጣው የባሕላዊ ትስስር አንዱ መገለጫ ነው" ብለዋል።
በርካታ ኢትዮጵያውያን ስለ ቻይና ቋንቋ እና ባሕል ለማወቅ ፍላጎት እያሳዩ እንደሆነም ተነግሯል፡፡
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X