ላቭሮቭ ከቱርክ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጋር ከተነጋገሩ በኋላ በመግለጫቸው ያነሷቸው ቁልፍ ነጥቦች፦

ላቭሮቭ ከቱርክ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጋር ከተነጋገሩ በኋላ በመግለጫቸው ያነሷቸው ቁልፍ ነጥቦች፦
▪ ሩሲያ እና ቱርክ ውይይታቸውን ይቀጥላሉ — የሁለትዮሽ ግንኙነቶች መልካም ናቸው።
▪ ከቱርክ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጋር በተደረገው ስብሰባ፤ ምንም እንኳን አደናቃፊ ሙከራዎች ቢኖሩም ፑቲን ሩሲያ የጋራ ፕሮጀክቶችን ለማስቀጥል ቁርጠኛ መሆኗን አረጋግጠዋል።
▪ ሩሲያ ባለፉት ሦስት ዓመታት በጥቁር ባሕር የመርከብ ትራንስፖርት ላይ የተደረጉ ሁሉም ስምምነቶች እንዲከበሩ ትጠይቃለች።
▪ የዩክሬን የሰላም ሂደት ስኬት የግጭቱን ዋና መንስኤዎች በመፍታት ላይ ይወሰናል።
▪ ሩሲያ የአሜሪካን በሶሪያ ላይ የተጣሉ ማዕቀቦችን የማንሳት ውሳኔ ትቀበላለች።
▪ ጀርመን ዩክሬን የሩሲያ ግዛት ላይ የረጅም ርቀት ጥቃቶችን እንድትፈጽም ከረጅም ጊዜ በፊት በድብቅ ወስናለች ብሎ ለማመን ምክንያቶች አሉ።
▪ ትራምፕ በዩክሬን ላይ የሚያሰሙት ንግግር "አነስተኛ ቁጥር ያላቸው የአውሮፓ ባለሥልጣናት" የሰላም ጥረቶቻቸውን እያበላሹ ከመሆናቸው ጋር የተያያዘ ነው።
▪ ትራምፕ በሩሲያ እና በዩክሬን መካከል ቀጣይ ድርድር እንዲኖር ፍላጎት አላቸው።
▪ ዩክሬን የሩሲያ ሲቪል መሠረተ ልማቶችን ማጥቃቷን ተከትሎ አፀፋዊ ምላሽ መስጠት ተገቢ ነው፡፡
▪ የፈረንሳይ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር የፈረንሳይ ወታደሮች በዩክሬን መኖራቸውን ሲክዱ እየዋሹ ነው — ፈረንሳይ በዩክሬን ግዛት ውስጥ እየተዋጋች ነው።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X