- Sputnik አፍሪካ, 1920
The Rising South
የዓለም አቀፍ የኃይል ሚዛን እየተቀየረ ባለበት በዚህ ወቅት - ኢትዮጵያን፣ አፍሪካን እና ሌሎችን የሚቀርጹ የፖለቲካ፣ የኢኮኖሚ እና የማህበራዊ ሃይሎች ወደምንመለከትበት ወደ “ራይዚንግ ሳዉዝ” እንኳን በደህና መጡ፡፡ ደቡባዊ አመለካከቶችን ወደ ዓለም አቀፋዊ ውይይት መድረክ ስናቀርብ የአሰላሳዮችን ፣ የመሪዎችን እና የለዉጥ ፈጣሪዎችን ሃሳብ ያድምጡ።

ብሪክስ:- የዓለም አቀፉን ንግድ እና ኢንቨስትመንት ጨዋታ ቀያሪ

ብሪክስ:- የዓለም አቀፉን ንግድ እና ኢንቨስትመንት ጨዋታ ቀያሪ
ሰብስክራይብ
"የብሪክስ ስኬት በመላው ዓለም የሚገኙ በቢሊዮን የሚቆጠሩ ሰዎችን ሕይወት ያሻሽላል።" ሲሉ በኢትዮጵያ የፋይናንስ ፎረም ላይ የተገኙት የ ሲቢኢ ካፒታል ኢንቨስትመንት ባንክ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ዘመዴነህ ንጋቱ ተናገሩ።

ኢትዮጵያ አባል የሆነችበት ይህ ህብረት "በዓለም አቀፍ ንግድ እና ኢንቨስትመንት ላይ ሚዛን የሚፈጥር ነው" ብለው በአጽንኦት ተናግረዋል። "ለአብነት ያህል የብሪክስ ባንክን ብንወስድ በማደግ ላይ ላሉ ገበያዎች እጅግ አስፈላጊ ለሆነው መጠነ-ሰፊ የመሠረተ-ልማት ግንባታ ፋይናንስ የሚያቀርብ ነው።" በማለት አክለዋል።

🎤 በፎረሙ ላይ የተሳተፉት የፋይናንስ ባለሙያው አቶ ጌታቸው ባሻህውረድ, የባንክ አማካሪው አቶ አስራት በትሩ እና የኢቲስዊች ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ ይልበስ አዲስ ተጨማሪ ሀሳቦችን ሰጥተዋል:-
📲 የዲጂታል ፋይናንስ አብዮት:- የብሎክቼይን ቴክኖሎጂ የገንዘብ ዝውውርን ፈጣን, አስተማማኝ እና ብቁ አድርጎታል።
🌐 ዓለምአቀፋዊ ተሳትፎ:- የኢትዮጵያን ገበያ ለውጪ ባንኮች መክፈት ውድድር, ካፒታል እና የፈጠራ ክህሎትን ስለሚያመጣ የሀገር ውስጥ ባንኮች ራሳቸውን ማብቃት ይኖርባቸዋል።
🎧 ስለኢትዮጵያ የፋይናንስ ማሻሻያ እንዲሁም ይዟቸው ስለሚመጣቸው ዕድሎች የበለጠ ለማወቅ ይህንን የራይዚንግ ሳውዝ ፖድካስት ሙሉውን ፕሮግራም በመከታተል የለውጡ አካል ይሁኑ።
አዳዲስ ዜናዎች
0