የሩሲያ ጦር በኪዬቭ አገዛዝ ለሚሰነዘሩ ማናቸውም የሽብር ጥቃቶች እና ትንኮሳዎች ምላሽ መስጠቱን እንደሚቀጥል የመከላከያ ሚኒስቴር አስታወቀ

© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱየሩሲያ ጦር በኪዬቭ አገዛዝ ለሚሰነዘሩ ማናቸውም የሽብር ጥቃቶች እና ትንኮሳዎች ምላሽ መስጠቱን እንደሚቀጥል የመከላከያ ሚኒስቴር አስታወቀ
የሩሲያ ጦር በኪዬቭ አገዛዝ ለሚሰነዘሩ ማናቸውም የሽብር ጥቃቶች እና ትንኮሳዎች ምላሽ መስጠቱን እንደሚቀጥል የመከላከያ ሚኒስቴር አስታወቀ - Sputnik አፍሪካ, 1920, 27.05.2025
ሰብስክራይብ

የሩሲያ ጦር በኪዬቭ አገዛዝ ለሚሰነዘሩ ማናቸውም የሽብር ጥቃቶች እና ትንኮሳዎች ምላሽ መስጠቱን እንደሚቀጥል የመከላከያ ሚኒስቴር አስታወቀ

ከሚኒስቴሩ መግለጫ የተገኙ ዋና ዋና ነጥቦች፦

◻የጥቃቶቹ ኢላማዎች የዩክሬን ወታደራዊ ተቋማት እና ወታደራዊ-ኢንዱስትሪ ኮምፕሌክስ ብቻ ናቸው።

◻የሩሲያ ወታደራዊ ተቋማት ላይ ያነጣጠሩ ጥቃቶች ዩክሬን በሩሲያ ሲቪል ተቋማት ላይ ለፈፀመቻቸው ጥቃቶች የተሰጠ ምላሽ ነው።

◻ከግንቦት 12 ጀምሮ በአጠቃላይ 2 ሺህ 331 ድሮኖች የተመቱ ሲሆን ከእነዚህ ውስጥ 1 ሺህ 465 ድሮኖች ከልዩ ወታደራዊ ኦፕሬሽን ክልል ውጪ የተመቱ ናቸው።

የሩሲያ ጦር አጠቃላይ ኢላማዎች፡-

◻በዲኔፕሮፔትሮቭስክ ክልል የሚገኘው ኦዘርኖዬ የአየር ማረፊያ እና የጥይት ማከማቻዎች፡፡

◻በክመልኒትስኪ ክልል የሚገኘው የስታሮኮንስታንቲኖቭ የአየር ማረፊያ መሠረተ ልማት፡፡

◻በካርኮቭ ክልል እና በዶኔትስክ ሕዝቦች ሪፐብሊክ የሚገኙ የጥይት ማከማቻዎች እንዲሁም በኦዴሳ ክልል የኤስ-300 ከአየር-ወደ-አየር ሚሳኤል ስርዓት መቆጣጠሪያ ቦታ፡፡

◻በዶኔትስክ ሕዝቦች ሪፐብሊክ በስቪያቶጎርስክ አቅራቢያ የሚገኝ ጊዜያዊ የቅጥረኞች ጦር ሰፈር እና በካርኮቭ ክልል የዩክሬን ወታደራዊ ቡድን የጥይት ማከማቻ፡፡

◻በክሪቮይ ሮግ እና በኒኮላይቭ ክልሎች የፓቭሎግራድ ኬሚካል ፋብሪካ፣ የአውሮፕላን ጥገና ማዕከል እና የአየር መከላከያ ራዳር ጣቢያዎች።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0