የአፍሪካ ልማት ባንክ አዲስ ፕሬዝዳንት ሊመርጥ ነው
19:36 26.05.2025 (የተሻሻለ: 19:54 26.05.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
የአፍሪካ ልማት ባንክ አዲስ ፕሬዝዳንት ሊመርጥ ነው
ባንኩ አዲስ አስተዳዳሪ ለመምረጥ ሐሙስ ዕለት በኮትዲቯር የሚቀመጠው አሜሪካ የአበዳሪውን የ555 ሚሊየን ዶላር ፈንድ አቋርጣለሁ ባለችበት ወቅት ነው።
የመገናኛ ብዙኃን ዘገባዎች እንደሚያመለክቱት ለአፍሪካ የሚደረገው እርዳታ እየቀነሰ በመምጣቱ እና ቀረጥን ጨምሮ የአሜሪካ ፖሊሲዎች የኢኮኖሚ ችግሮችን እያባባሱ በመምጣታቸው አዲሱ ፕሬዝዳንት ድጋፍ ለማግኘት ፊታቸውን ወደ ሌላ ቦታ ማዞር ሊኖርባቸው ይችላል።
ቻይና፣ ሳዑዲ ዓረቢያ፣ የተባበሩት ዓረብ ኤሚሬቶች ወይም ከሌሎች የአፍሪካ ሀገራት የሚገኝ የተጠናከረ ድጋፍ በአማራጭነት ተነስቷል።
ለፕሬዝዳንትነት የሞሪታኒያ፣ ዛምቢያ፣ ሴኔጋል፣ ደቡብ አፍሪካ እና ቻድ እጩዎች ይወዳደራሉ።
በሰው ሰራሽ አስተውሎት የበለፀገ ምስል
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X