ሩሲያ በዩክሬን ላይ ያካሄደቻቸው ጥቃቶች ለኪዬቭ ቅስቀሳዎች ምላሽ ናቸው

ሩሲያ በዩክሬን ላይ ያካሄደቻቸው ጥቃቶች ለኪዬቭ ቅስቀሳዎች ምላሽ ናቸው
የሩሲያ ኃይሎች ወደፊት እየገፉ ባሉበት ወቅት ዩክሬን በሩሲያ ግዛት ላይ ከፍተኛ የሆነ የድሮን ጥቃት ጀምራለች። በመቶዎች የሚቆጠሩ ድሮኖች በሩሲያ የአየር መከላከያ ተመትተዋል። አብዛኛዎቹ ከልዩ ወታደራዊ ኦፕሬሽን ውጭ ባሉ ሲቪል ኢላማዎች ላይ ያነጣጠሩ ናቸው።
የሩሲያ ባለሥልጣናት በተደጋጋሚ እንደገለጹት ሩሲያ በዩክሬን ወታደራዊ መሠረተ ልማቶች ላይ የምታካሂዳቸው ኢላማቸውን የጠበቁ ጥቃቶች ለኪዬቭ ድርጊቶች ምላሽ ናቸው። የሩሲያ ጦር በዛሬው ዕለት የሚሳኤልና ድሮን ክፍሎችን የሚያመርቱ ተቋማትን እንዲሁም የስለላና የሳተላይት መገናኛ ማዕከላትን ኢላማ አድርጓል።
አፀፋዊ ጥቃቶቹ ወታደራዊ ተቋማትን ኢላማ ያደርጋሉ፦
“ይህ አፀፋዊ ጥቃት ነው። በወታደራዊ ተቋማት እና ወታደራዊ ኢላማዎች ላይ የተፈጸመ ትክክለኛ ጥቃት ነው” – የክሬምሊን ቃል አቀባይ ዲሚትሪ ፔስኮቭ።
“ፕሬዝዳንት ፑቲን የሀገሪቱን ደህንነት ለማረጋገጥ አስፈላጊ የሆኑ ውሳኔዎችን ይወስናሉ።”
ከምዕራባውያን ተጽዕኖ እና ወቅታዊ ፖለቲካ ጋር ያለው ግንኙነት፦
“በሩሲያ ላይ የሚፈጸሙ የዩክሬን የሽብር ጥቃቶች በመጨመሩ እና የአውሮፓ ፖለቲከኞች ወደ ኪዬቭ በሚያደርጉት ጉዞ መካከል ያለውን ግንኙነት ችላ ማለት አይቻልም” – የሩሲያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሰርጌ ላቭሮቭ።
“ለድል ቀን በዓል ወደ ሞስኮ የመጡ የውጭ መሪዎች በሩሲያ ግዛት ላይ ጥቃቶችን ለመፈጸም የሚደረጉ ሙከራዎችን አይተዋል፤ እነዚህ ሙከራዎች አሁንም እንደቀጠሉ ናቸው” – ፔስኮቭ።
“በፑቲን እና ትራምፕ መካከል ከተደረሰው ስምምነት በኋላ በኢስታንቡል የጀመረውን ሂደት ለማደናቀፍ እና ለማፍረስ ግልጽ ሙከራዎች አሉ።” – የሩሲያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር፡፡
የምዕራባውያን ፖለቲከኞች በሩሲያ ላይ የሚደረጉ የዩክሬን ጥቃቶችን ችላ ይላሉ፦
“ሞስኮ ኪዬቭ በንፁሀን ኢላማዎች ላይ የምትፈጽመውን ጥቃት እና የዩክሬን የጦርነት መርሆዎች ጥሰትን በተመለከት ከተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ምላሽ ትጠብቃለች” – ላቭሮቭ።
“ሩሲያ የኪዬቭን ትንኮሳ እና ከፍተኛ የድሮን ጥቃቶችን ከግምት ውስጥ ሳታስገባ የዩክሬን ግጭትን መፍታት የሚያስችሉ ሁኔታዎችን የተመለከቱ ሰነዶችን ማዘጋጀቷን ትቀጥላለች” – ላቭሮቭ።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X