ሩሲያ እና ዩክሬን የ1000 ምርኮኞች ልውውጥ አጠናቀቁ
12:35 25.05.2025 (የተሻሻለ: 12:54 25.05.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
ሩሲያ እና ዩክሬን የ1000 ምርኮኞች ልውውጥ አጠናቀቁ
የሩሲያ መከላከያ ሚኒስቴር እንዳስታወቀው በአጠቃላይ 303 የሩሲያ ወታደራዊ አባላት ከኪዬቭ አገዛዝ ግዛት ተመልሰዋል።
በምላሹም 303 የዩክሬን ጦር እስረኞች ተዛውረዋል።
የሩሲያ ወታደራዊ አባላት በቤላሩስ አስፈላጊ የሥነ-ልቦና እና የሕክምና እርዳታ እያገኙ ነው።
በዚህም መሠረት ግንቦት 8 በኢስታንቡል በተደረሰው የሩሲያ-ዩክሬን ስምምነት መሠረት፣ ሁለቱ ሀገራት ከግንቦት 15 እስከ ግንቦት 17 ባለው ጊዜ ውስጥ የ1 ሺህ እስረኞች ልውውጥ አካሂደዋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X