የኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ጥሩ ቁመና ላይ ይገኛል ሲሉ ሚኒስትር ደኤታው ተናገሩ

© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱየኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ጥሩ ቁመና ላይ ይገኛል ሲሉ ሚኒስትር ደኤታው ተናገሩ
የኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ጥሩ ቁመና ላይ ይገኛል ሲሉ ሚኒስትር ደኤታው ተናገሩ - Sputnik አፍሪካ, 1920, 23.05.2025
ሰብስክራይብ

የኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ጥሩ ቁመና ላይ ይገኛል ሲሉ ሚኒስትር ደኤታው ተናገሩ

በጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት የብሔራዊ ደህንነት ጉዳዮች ሚኒስትር ደኤታ ቀንአ ያደታ ሀገሪቱ በአፍሪካ ቀንድ የሚታዩ የጸጥታ ችግሮችን በመፍታት ረገድ ቁልፍ እንደሆነች ገልፀው ሚናዋንም እየተወጣች ነው ብለዋል።

ባለሥልጣኑ ከሶስተኛው የአፍሪካ ቀንድ እና የኤደን ባሕረ ሰላጤ ውይይት ጎን ለጎን ከስፑትኒክ አፍሪካ ጋር ባደረጉት ቃለምልልስ የተናገሩት ነው።

አክለውም የኢትዮጵያ ብሪክስን መቀላቀል የሀገሪቱን ማንሰራራት የሚያመለክት እንደሆነ ተናግረዋል።

"የብሪክስ አባል መሆኗ እጅግ በጣም ወሳኝ ነው፡፡...ኢትዮጵያ ኢኮኖሚያዊ እና ፖለቲካዊ ጠቀሜታን ታገኛለች፡፡ ኢትዮጵያ ወደ ፊት እየተራመደች እንደሆነም ያሳያል፡፡ ባለፉት ሰባት ዓመታት ነው እንደዚህ ዓይነት ስኬታማ ለውጦችን እያሳያች የመጣችው" ሲሉ አብራርተዋል።

በሌላ በኩል የአፍሪካ ቀንድ እና የኤደን ባሕረ ሰላጤ ሀገራት ትብብር እና ቅንጅት ለቀጣናው ሰላም እና ደህንነት እንዲሁም ልማት አስተዋጽኦ እንዳለው ተናግረዋል፡፡

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0