አሰላ የንፋስ ኃይል ማመንጫ ለኢትዮጵያ ብሔራዊ የኃይል ቋት የመጀመሪያውን ኃይል ማቅረብ ጀመረ
13:55 23.05.2025 (የተሻሻለ: 14:04 23.05.2025)
© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱአሰላ የንፋስ ኃይል ማመንጫ ለኢትዮጵያ ብሔራዊ የኃይል ቋት የመጀመሪያውን ኃይል ማቅረብ ጀመረ

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
አሰላ የንፋስ ኃይል ማመንጫ ለኢትዮጵያ ብሔራዊ የኃይል ቋት የመጀመሪያውን ኃይል ማቅረብ ጀመረ
ፕሮጀክቱ በሦስት ተርባይኖች 100 ሜጋ ዋት የንፋስ ኃይል ያመነጫል ተብሎ ይጠበቃል፡፡
በታህሳስ 2018፣ 29 ተርባይኖች ሙሉ በሙሉ ወደ ሥራ ሲገቡ በየዓመቱ ከ300 ጊጋ ዋት ሰዓት በላይ ንጹህና ዘላቂ ኃይል ያመነጫል ተብሏል።
ይህም ከ140 ሺህ በላይ አባወራዎችን የኤሌክትሪክ ፍላጎት ለማሟላት በቂ ነው ሲል የገንዘብ ሚኒስቴር አስታውቋል።
ፕሮጀክቱ ታዳሽ ኃይልን ወደ ግሪድ በማስገባት የሀገሪቱን ኢኮኖሚ ለማሳደግ እና ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር ኢኮኖሚ ለመገንባት እንደሚያስችል ተነግሯል፡፡
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X