በሩሲያ እና በዩክሬን መካከል ሁለተኛ ዙር ድርድር እንደሚካሄድ ላቭሮቭ አረጋገጡ

ሰብስክራይብ

በሩሲያ እና በዩክሬን መካከል ሁለተኛ ዙር ድርድር እንደሚካሄድ ላቭሮቭ አረጋገጡ

የሩሲያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ተጨማሪ መግለጫዎች፦

🟠 ዩክሬን ሁለተኛ ዙር ድርድር እንደሚኖር አረጋግጣለች፤ ነገር ግን የድርድሩ ቀን ሆነ ሥፍራው እስካሁን አልተወሰነም።

🟠 ቫቲካን ለሩሲያ እና ዩክሬን የድርድር ሥፍራ ሆና መመረጧ "ተገቢ አይደለም"።

🟠 ዩክሬን የአሜሪካ ድጋፍ ዘላቂ ይሆናል ብላ ጠብቃ ነበር፤ ነገር ግን ትራምፕ "የእኔ ጦርነት አይደለም" የሚል አቋም ይዘዋል።

🟠 ሩሲያ የዩክሬን ግጭትን ለመፍታት የሚያስችል የመግባቢያ ሰነድ እያዘጋጀች ነው።

🟠 የዩክሬንን ግጭት ለመፍታት ቀላሉ መንገድ ኪዬቭ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ቻርተርን በቀጥታ የሚጥሱ ሕጎችን እንድትሽር መጠየቅ ነው።

🟠 ከሩሲያ ጋር ከጥንካሬ አቋም በመነሳት መነጋገር ፋይዳ የለውም።

🟠 የዘለንስኪ ሕጋዊነት ጥያቄ የሰላም ሰነዶች ሲፈረሙ ወሳኝ ይሆናል።

🟠 ሩሲያ የግጭቱን ዋና መንስኤዎች የሚፈታ የሰላም ድርድር ከዩክሬን ጋር ለማድረግ ሁልጊዜም ዝግጁ ነች፤ ግኑኝነቶችን ሸሽታ አታውቅም።

🟠 ዘለንስኪ የመምራት ብቃት እንደሌለው ግልፅ ነው።

🟠 ሩሲያ በዩክሬን የሚኖሩ ሰዎች በዘለንስኪ ጁንታ በተጫኑ ሕጎች ሥር እንዲኖሩ አትፈቅድም።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0