በዩኔስኮ የተመዘገቡት የኮንሶ አምባ መንደሮች ቅርስነታቸውን የመልቀቅ አደጋ ተጋርጦባቸዋል ተባለ

© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱበዩኔስኮ የተመዘገቡት የኮንሶ አምባ መንደሮች ቅርስነታቸውን የመልቀቅ አደጋ ተጋርጦባቸዋል ተባለ
በዩኔስኮ የተመዘገቡት የኮንሶ አምባ መንደሮች ቅርስነታቸውን የመልቀቅ አደጋ ተጋርጦባቸዋል ተባለ - Sputnik አፍሪካ, 1920, 23.05.2025
ሰብስክራይብ

 በዩኔስኮ የተመዘገቡት የኮንሶ አምባ መንደሮች ቅርስነታቸውን የመልቀቅ አደጋ ተጋርጦባቸዋል ተባለ

በአምባ መንደሮቹ የሚገኙ ጎጆ ቤቶችን ቆርቆሮ በማልበስ ቅርስነታቸውን እንዲለቁ እየተደረገ ነው ተብሏል።

አሁን ላይ 50 በመቶ የሚሆኑት ቆርቆሮ ለብሰዋል መባሉን የአካባቢውን የባህል እና ቱሪዝም ቢሮ ጠቅሶ የሀገር ውስጥ ሚዲያ ዘግቧል።

የአካባቢው ማሕበረሰብ ለጣሪያ ክዳን የሚጠቀምበትን የሳር ግብዐት ለማቅረብ እንቅስቃሴዎች በሚመለከታቸው አካላት መጀመሩም ነው የተጠቀሰው።

እ.አ.አ በ2011 በዓለም ቅርስነት የተመዘገበው የኮንሶ መልክዓ ምድር በካብ የታጠሩ መንደሮች፣ ባህላዊ ጎጆዎች፣ ጥብቅ ደኖች፣ ሐውልቶች እና ኩሬዎችን ይዟል።

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0