ዩናይትድ ኪንግደም እና ሞሪሺየስ የቻጎስ ደሴቶች ስምምነትን ሐሙስ እንደሚያጠናቅቁ ተገለፀ

© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱዩናይትድ ኪንግደም እና ሞሪሺየስ የቻጎስ ደሴቶች ስምምነትን ሐሙስ እንደሚያጠናቅቁ ተገለፀ
ዩናይትድ ኪንግደም እና ሞሪሺየስ የቻጎስ ደሴቶች ስምምነትን ሐሙስ እንደሚያጠናቅቁ ተገለፀ - Sputnik አፍሪካ, 1920, 22.05.2025
ሰብስክራይብ

ዩናይትድ ኪንግደም እና ሞሪሺየስ የቻጎስ ደሴቶች ስምምነትን ሐሙስ እንደሚያጠናቅቁ ተገለፀ

ጠቅላይ ሚኒስትር ኪር ስታርመር ይገኙበታል የተባለው የቻጎስ ደሴቶችን የማዘዋወር ሥነ-ሥርዓት በቨርችዋል እንደሚካሄድ የብሪታንያ ሚዲያ ዘግቧል።

ሞሪሺየስ ደሴቶቹን እንደገና የምትቆጣጠር ቢሆንም ዩናይትድ ኪንግደም እና አሜሪካ በዲዬጎ ጋርሺያ ላይ ያላቸውን ስትራቴጂካዊ የጦር ሰፈር ቢያንስ ለ99 ዓመታት ይዘው ይቆያሉ። በድጋሚ ለተጨማሪ 40 ዓመት የማራዘም አማራጭም አላቸው።

ስምምነቱ ባለፈው ህዳር የተመረጡት የሞሪሸስ ጠቅላይ ሚኒስትር ናቪን ራምጎላም ከገንዘብ ማካካሻ ጋር በተያያዘ የመነሻ ውሎችን ውድቅ ካደረጉ በኋላ ለወራት የተካሄደውን ድርድር ተከትሎ የመጣ ነው። ዩናይትድ ኪንግደም የጦር ሰፈሩን መጠቀሟን ለመቀጠል ለሞሪሸስ 9 ቢሊዮን ፓውንድ (12 ቢሊዮን ዶላር) ትከፍላለች።

ℹ ሞሪሸስ ለበርካታ አስርት ዓመታት እንግሊዝ በቻጎስ ደሴቶች ላይ አለኝ የምትለውን ሉዓላዊነት ስትቃወም ቆይታለች። ሆኖም የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ጠቅላላ ጉባኤ ለንደን በደሴቶቹ ላይ ያላትን ቁጥጥር እንድታቆም የሚጠይቅ ውሳኔ ያስተላለፈው እ.አ.አ በ2019 ነበር።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0