ዩናይትድ ኪንግደም እና ሞሪሺየስ የቻጎስ ደሴቶች ስምምነትን ሐሙስ እንደሚያጠናቅቁ ተገለፀ
17:39 22.05.2025 (የተሻሻለ: 17:54 22.05.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
ዩናይትድ ኪንግደም እና ሞሪሺየስ የቻጎስ ደሴቶች ስምምነትን ሐሙስ እንደሚያጠናቅቁ ተገለፀ
ጠቅላይ ሚኒስትር ኪር ስታርመር ይገኙበታል የተባለው የቻጎስ ደሴቶችን የማዘዋወር ሥነ-ሥርዓት በቨርችዋል እንደሚካሄድ የብሪታንያ ሚዲያ ዘግቧል።
ሞሪሺየስ ደሴቶቹን እንደገና የምትቆጣጠር ቢሆንም ዩናይትድ ኪንግደም እና አሜሪካ በዲዬጎ ጋርሺያ ላይ ያላቸውን ስትራቴጂካዊ የጦር ሰፈር ቢያንስ ለ99 ዓመታት ይዘው ይቆያሉ። በድጋሚ ለተጨማሪ 40 ዓመት የማራዘም አማራጭም አላቸው።
ስምምነቱ ባለፈው ህዳር የተመረጡት የሞሪሸስ ጠቅላይ ሚኒስትር ናቪን ራምጎላም ከገንዘብ ማካካሻ ጋር በተያያዘ የመነሻ ውሎችን ውድቅ ካደረጉ በኋላ ለወራት የተካሄደውን ድርድር ተከትሎ የመጣ ነው። ዩናይትድ ኪንግደም የጦር ሰፈሩን መጠቀሟን ለመቀጠል ለሞሪሸስ 9 ቢሊዮን ፓውንድ (12 ቢሊዮን ዶላር) ትከፍላለች።
ℹ ሞሪሸስ ለበርካታ አስርት ዓመታት እንግሊዝ በቻጎስ ደሴቶች ላይ አለኝ የምትለውን ሉዓላዊነት ስትቃወም ቆይታለች። ሆኖም የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ጠቅላላ ጉባኤ ለንደን በደሴቶቹ ላይ ያላትን ቁጥጥር እንድታቆም የሚጠይቅ ውሳኔ ያስተላለፈው እ.አ.አ በ2019 ነበር።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X