የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ባለ ስምንት ወለልና አንድ ሺህ መኪኖችን ማቆየት የሚችል የመኪና ማቆሚያ አስመረቀ
11:10 22.05.2025 (የተሻሻለ: 12:14 22.05.2025)
© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱየአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ባለ ስምንት ወለልና አንድ ሺህ መኪኖችን ማቆየት የሚችል የመኪና ማቆሚያ አስመረቀ

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ባለ ስምንት ወለልና አንድ ሺህ መኪኖችን ማቆየት የሚችል የመኪና ማቆሚያ አስመረቀ
ይህም በመዲናዋ ውስጥ የተገነቡትን የመኪና ማቆሚያዎች ቁጥር ወደ 150 ከፍ እንደሚያደርግ ከንቲባ አዳነች አቤቤ አስታውቀዋል።
ከለውጡ በፊት በመንግሥት የተገነቡ የፓርኪንግ ቦታዎች ብዛት 2 ብቻና ከ500 በላይ መኪኖችን የማቆም አቅም እንዳልነበራቸው በማሕበራዊ ገጻቸው ባጋሩት ፅሑፍ ጠቁመዋል።
ከንቲባዋ በአጠቃላይ 35 ሺህ ተሽከርካሪዎችን በአንድ ጊዜ ማቆም የሚችሉ እንዲሁም 49 ተርሚናሎች መገንባታቸውን ገልጸዋል።
አዲሱ የመኪና ማቆሚያ ምቹ፣ ደህንነቱ የተጠበቀ እና ዘመናዊ ቴክኖሎጂ የተገጠመለት እንዲሁም የሕዝቡን እንግልት የሚቀንስ መሆኑ ተገልጿል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X
© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱየአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ባለ ስምንት ወለልና አንድ ሺህ መኪኖችን ማቆየት የሚችል የመኪና ማቆሚያ አስመረቀ

© telegram sputnik_ethiopia
/