የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ባለ ስምንት ወለልና አንድ ሺህ መኪኖችን ማቆየት የሚችል የመኪና ማቆሚያ አስመረቀ

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ባለ ስምንት ወለልና አንድ ሺህ መኪኖችን ማቆየት የሚችል የመኪና ማቆሚያ አስመረቀ
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ባለ ስምንት ወለልና አንድ ሺህ መኪኖችን ማቆየት የሚችል የመኪና ማቆሚያ አስመረቀ - Sputnik አፍሪካ, 1920, 22.05.2025
ሰብስክራይብ
ይህም በመዲናዋ ውስጥ የተገነቡትን የመኪና ማቆሚያዎች ቁጥር ወደ 150 ከፍ እንደሚያደርግ ከንቲባ አዳነች አቤቤ አስታውቀዋል።
ከለውጡ በፊት በመንግሥት የተገነቡ የፓርኪንግ ቦታዎች ብዛት 2 ብቻና ከ500 በላይ መኪኖችን የማቆም አቅም እንዳልነበራቸው በማሕበራዊ ገጻቸው ባጋሩት ፅሑፍ ጠቁመዋል።
ከንቲባዋ በአጠቃላይ 35 ሺህ ተሽከርካሪዎችን በአንድ ጊዜ ማቆም የሚችሉ እንዲሁም 49 ተርሚናሎች መገንባታቸውን ገልጸዋል።
አዲሱ የመኪና ማቆሚያ ምቹ፣ ደህንነቱ የተጠበቀ እና ዘመናዊ ቴክኖሎጂ የተገጠመለት እንዲሁም የሕዝቡን እንግልት የሚቀንስ መሆኑ ተገልጿል።
አዳዲስ ዜናዎች
0