ሩሲያ በግጭት ምክንያት ጠፍቶ የነበረውን ቁልፍ የጂኦሎጂካል መረጃ ለሱዳን አስረከበች
19:11 21.05.2025 (የተሻሻለ: 12:14 22.05.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
ሩሲያ በግጭት ምክንያት ጠፍቶ የነበረውን ቁልፍ የጂኦሎጂካል መረጃ ለሱዳን አስረከበች
በሱዳን-ሩሲያ የጋራ የሚኒስትሮች ኮሚቴ ስብሰባ ወቅት ሁለት የጂኦሎጂካል አትላሶች እና የቴክኒክ ሪፖርቶች ለሱዳን ማዕድን ሚኒስቴር ተሰጥተዋል፡፡ እነዚህ መረጃዎች በሱዳን ጦርነት ወቅት የወደሙትን የጂኦሎጂካል መረጃዎች የሚተኩ መሆናቸው ተገልጿል።
ርክክቡ የተካሄደው የሱዳን ማዕድን ኃብት ምክትል ፀሐፊ ዶ/ር ሂንድ ሲዲቅ በካዛን የኢኮኖሚ ፎረም ወቅት የጋራ ፕሮጀክት መረጃዎችን የዲጂታል ቅጂዎች ከጠየቁ በኋላ ነው። ሩሲያ የመረጃዎቸን የወረቀት ቅጂዎች በቦታው ያቀረበች ሲሆን ዲጂታል ቅጂዎችም በቅርቡ እንደሚተላለፉ ቃል ገብታለች።
◾ውይይቶች በሱዳን ሊደረጉ የሚችሉ የክሮሚየም እና ማንጋኒዝ ኢንቨስትመንቶችን ያካተቱ ናቸው።
◾የሱዳን ልዑካን ቡድን በመጪው ሰኔ ለሚካሄደው የኮሚቴው ስብሰባ ውይይት የሚደረግባቸውን የትብብር ሀሳቦች አቅርቧል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X