ሶማሌ ክልል የወጣቶችን የጋብቻ ጫና ለመቀነስ አላስፈላጊ የጋብቻ ወጪዎችን የሚከለክል ደንብ አጸደቀ
18:30 21.05.2025 (የተሻሻለ: 19:34 21.05.2025)
© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱሶማሌ ክልል የወጣቶችን የጋብቻ ጫና ለመቀነስ አላስፈላጊ የጋብቻ ወጪዎችን የሚከለክል ደንብ አጸደቀ

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
ሶማሌ ክልል የወጣቶችን የጋብቻ ጫና ለመቀነስ አላስፈላጊ የጋብቻ ወጪዎችን የሚከለክል ደንብ አጸደቀ
የክልሉ የሐይማኖት እና ባህላዊ መሪዎች ጋብቻን ተከትሎ የሚወጣውን የተጋነነ ወጪ በመቀነስ ወጣቶች ከትዳር እንዳይሸሹ ማድረግ ያስፈልጋል ብለዋል።
የሀማሮ የእስልምና ምክር ቤት ከጋብቻ በፊት ግመል ማረድ እንዲሁም ሴቶች በሚታጩበት ወቅት የሚሰጡ የተለያዩ ውድ ስጦታዎች ቅዱሱ የጋብቻ ሥነ-ሥርዓት አስገዳጅ የገንዘብ ጫና እንዲፈጥር አድርጎታል በሚል ስጋት አዋጁ ሊወጣ ችሏል ብሏል።
አዋጁ በተለይም ገበቲ ተብሎ የሚጠራውን እና የሙሽራው ቤተሰቦች ለሙሽራዋ ጎረቤቶች የሚያከናውኑት ተመላሽ የግመል ጥሎሽ ስርዓት ማሕበራዊ ጫናን ያሳድራል በማለት ማስቀረቱ ተዘግቧል።
የክልሉ የሐይማኖት እና የባህላዊ መሪዎች ሕጉን መጣስ የገንዘብ እና እስር ቅጣት ሊያስከትል እንደሚችል አስጠንቅቀዋል።
በሰው ሰራሽ አስተውሎት የበለፀገ ምስል
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X