የኢትዮጵያ ዓመታዊ የሲሚንቶ ምርት 20 ሚሊየን ሜትሪክ ቶን ደረሰ
11:35 21.05.2025 (የተሻሻለ: 12:14 21.05.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
የኢትዮጵያ ዓመታዊ የሲሚንቶ ምርት 20 ሚሊየን ሜትሪክ ቶን ደረሰ
የማዕድን ሚኒስትሩ ሀብታሙ ተገኝ የነባር ፋብሪካዎችን ምርታማነት በማሳደግና አዳዲሶችን ወደ ሥራ በማስገባት ከሀገር ውስጥ በተጨማሪ ለጎረቤት ሀገራት ሲሚንቶ ማቅረብ የሚያስችል አቅም እየተፈጠረ ነው ብለዋል።
አክለውም አራት የድንጋይ ከሰል ማቀነባበሪያ ፋብሪካዎችን ወደ ሥራ በማስገባት የሲሚንቶ አምራቾችን አቅም የማሳደግ ሥራ እየተሠራ እንደሚገኝ ገልጸዋል።
ለኮንስትራክሽን ኢንዱስትሪ የግብዓት አቅርቦት ምላሽ ለመስጠት በብረት፣ እምነ በረድ፣ ሲሚንቶና ሌሎች መስኮች እደገቶች እየተመዘገቡ እንደሆነም ተናግረዋል።
በድሬዳዋ ከተማ የተገነባው የፓዮኔር ሲሚንቶ ማኑፋክቸሪንግ ማስፋፊያ ፕሮጀክት በትናትናው እለት በፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀሥላሴ ተመርቆ ተከፍቷል፡፡
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X
© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱ

© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱ
