የኢትዮጵያ ዓመታዊ የሲሚንቶ ምርት 20 ሚሊየን ሜትሪክ ቶን ደረሰ
11:35 21.05.2025 (የተሻሻለ: 12:14 21.05.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
የኢትዮጵያ ዓመታዊ የሲሚንቶ ምርት 20 ሚሊየን ሜትሪክ ቶን ደረሰ
የማዕድን ሚኒስትሩ ሀብታሙ ተገኝ የነባር ፋብሪካዎችን ምርታማነት በማሳደግና አዳዲሶችን ወደ ሥራ በማስገባት ከሀገር ውስጥ በተጨማሪ ለጎረቤት ሀገራት ሲሚንቶ ማቅረብ የሚያስችል አቅም እየተፈጠረ ነው ብለዋል።
አክለውም አራት የድንጋይ ከሰል ማቀነባበሪያ ፋብሪካዎችን ወደ ሥራ በማስገባት የሲሚንቶ አምራቾችን አቅም የማሳደግ ሥራ እየተሠራ እንደሚገኝ ገልጸዋል።
ለኮንስትራክሽን ኢንዱስትሪ የግብዓት አቅርቦት ምላሽ ለመስጠት በብረት፣ እምነ በረድ፣ ሲሚንቶና ሌሎች መስኮች እደገቶች እየተመዘገቡ እንደሆነም ተናግረዋል።
በድሬዳዋ ከተማ የተገነባው የፓዮኔር ሲሚንቶ ማኑፋክቸሪንግ ማስፋፊያ ፕሮጀክት በትናትናው እለት በፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀሥላሴ ተመርቆ ተከፍቷል፡፡
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X