ዓለም አቀፉ የፍትሕ ፍርድ ቤት በነዳጅ በበለፀገው የጊኒ ባህረ ሰላጤ የሚገኙ የሶስት ትናንሽ ደሴቶች ሉዓላዊነትን ለኢኳቶሪያል ጊኒ ሰጠ
18:00 20.05.2025 (የተሻሻለ: 18:24 20.05.2025)
© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱዓለም አቀፉ የፍትሕ ፍርድ ቤት በነዳጅ በበለፀገው የጊኒ ባህረ ሰላጤ የሚገኙ የሶስት ትናንሽ ደሴቶች ሉዓላዊነትን ለኢኳቶሪያል ጊኒ ሰጠ

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
ዓለም አቀፉ የፍትሕ ፍርድ ቤት በነዳጅ በበለፀገው የጊኒ ባህረ ሰላጤ የሚገኙ የሶስት ትናንሽ ደሴቶች ሉዓላዊነትን ለኢኳቶሪያል ጊኒ ሰጠ
ጋቦን እና ኢኳቶሪያል ጊኒ ላለፉት አስርት ዓመታት በደሴቶቹ የይገባኛል ጥያቄ ሲወዛገቡ ነበር።
ፍርድ ቤቱ በመጨረሻ አሳሪ ውሳኔው ጋቦን እ.ኤ.አ 1974 የተደርሰውን ስምምነት መሠረት አድርጋ ያነሳችውን የይገባኛል ጥያቄ ውድቅ በማድረግ፤ ኢኳቶሪያል ጊኒ እ.ኤ.አ በ1900 በቅኝ ግዛት ዘመን የተደረገ ስምምነትን መሠረት አድርጋ ያቀረበችውን ጥያቄ ተቀብሏል።
ውሳኔው ጋቦን ከ1972 ጀምሮ በያዘችው ምባኒዬ ደሴት ላይ ያሉ ወታደሮቿን እንድታስወጣ ይጠይቃል።
ውዝግቡ በ2000ዎቹ መጀመሪያ በእምቅ የባህር ውስጥ የነዳጅ ክምችቶች ምክንያት ዳግም ተቀስቅሶ በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የሽምግልና ሙከራ ከተደረገ በኋላ እ.ኤ.አ በ2016 በይፋ ለዓለም አቀፉ የፍትሕ ፍርድ ቤት ቀርቧል፡፡
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X