ቦትስዋና ፖለቲካዊ ጣልቃ ገብነት የሌለበት ዓለም አቀፍ ፍትህን የማስፈን ጥሪን ትደግፋለች ሲሉ የቦትሶዋና የፍትህ ሚኒስትር ተናገሩ

ሰብስክራይብ

ቦትስዋና ፖለቲካዊ ጣልቃ ገብነት የሌለበት ዓለም አቀፍ ፍትህን የማስፈን ጥሪን ትደግፋለች ሲሉ የቦትሶዋና የፍትህ ሚኒስትር ተናገሩ

ሚኒስትሩ ኔልሰን ራማኦትዋና በሩሲያ እና ሌሎች መሪነት ከዓለም አቀፍ የሕግ ስርዓቶች ፖለቲካዊ አድልኦን ለማስወገድ ለሚደረጉ ጥረቶችን ድጋፍ እንደሚሰጡ ገልጸዋል።

ከ13ኛው የሴንት ፒተርስበርግ ዓለም አቀፍ የሕግ መድረክ ጎን ለጎን ለስፑትኒክ አፍሪካ በሰጡት ቃል “ፍትሕ በቀለም አትለይም፤ ፍትሕ ለሁሉም ሰው እና አድልኦ አታደርግም” ብለዋል።

ራማኦትዋና ፍትሕ ለሀብታም ወይም ኃያል ሀገራት ማድላት እንደሌለባት አጽንኦት በመስጠት፤ ሁሉም መንግሥታት አካታች እና ለሁሉም እኩል የሆነ ስርዓት እንዲዘረጉ ጥሪ አቅርበዋል።

"ኃይል ላይ ያልተመሠረት መድልዎ የማያደርግ ስርዓት እንፈልጋለን።"

ዓለም አቀፉ ማሕበረሰብ ያለፉ ስህተቶቹን እንዲገመግም እና ፍትሐዊና ሚዛናዊ ዓለም አቀፍ የወንጀል ፍትህ ስርዓት እንዲዘረጋ ጥሪ አቅርበዋል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0