ዓለም አቀፍ ጎብኚዎች የኢትዮጵያን የቴክኖሎጂ ኤክስፖ አደነቁ

ዓለም አቀፍ ጎብኚዎች የኢትዮጵያን የቴክኖሎጂ ኤክስፖ አደነቁ
ዱባይ መቀመጫውን ባደረገው ሳንድቦክስ ሴኩሪቲ ዋና ሥራ አስፈጻሚ እና መስራች ራሁል ፑሮሂት "ለሰዎች ስለ ሳይበር ደህንነትና ሰው ሰራሽ አስተውሎት ማስተማርና ግንዛቤ ማስጨበጥ ያስፈልጋል" በማለት ኤክስፖው ብዙ ዕድሎች ያሉት ድንቅ ዝግጅት እንደሆነ ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግሯል።
የብሪክስ ሀገራት በእነዚህ መስኮች አዳዲስ ፈጠራዎችን እየፈጠሩ እንደሆነና ኢትዮጵያ አዲስ አባል እንደመሆኗ ከብሪክስ ጉባኤዎችና ከአባል ሀገራት ድጋፍ ብዙ ልታገኝ እንደምትችል አስረድቷል።
የቻይና የደህንነት ምርመራ ቴክኖሎጂ ኩባንያ ኑክቴክ የሀገር ውስጥ ሥራ አስኪያጅ ሶፊ ዣኦ የኢትዮጵያን ስትራቴጂካዊ ቦታ፣ የኢኮኖሚ ሀብት እና በቅርቡ የብሪክስ አባል መሆኗን አወድሳለች። ወደፊት ተጨማሪ የትብብር እና የጋራ እድገት እድሎች እንደሚኖሩም ግምቷን አስቀምጣለች።
በተጨማሪም የኢትዮጵያ መንግሥትን የዘመናዊነት እና የዲጂታል ግቦች በማድነቅ ኑክቴክ ለኢትዮጵያ የተሳካ ትብብር ድጋፍ እንደሚያደርግ ቃል ገብታለች።
በኢትዮጵያ ጥሩ የቴክኒክ እውቀት እና ጠንካራ የደህንነት ደረጃዎች ግንዛቤ እንዳለ ጠቅሳ፤ ይህም ለግንኙነት አመቺ እንደሆነና ኑክቴክ ለደህንነት መሳሪያዎቹ በቀላሉ ገበያ እንዲያገኝ ማስቻሉን ተናግራለች።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X