ሩሲያ እና ዩክሬን በኢስታንቡል ለድርድር መቀመጣቸው ለዓለም ሰላም መልካም ተስፋ ነው ሲሉ ኢትዮጵያዊው የፖለቲካ ሳይንስ ተመራማሪ ተናገሩ

© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱሩሲያ እና ዩክሬን በኢስታንቡል ለድርድር መቀመጣቸው ለዓለም ሰላም መልካም ተስፋ ነው ሲሉ ኢትዮጵያዊው የፖለቲካ ሳይንስ ተመራማሪ ተናገሩ
ሩሲያ እና ዩክሬን በኢስታንቡል ለድርድር መቀመጣቸው ለዓለም ሰላም መልካም ተስፋ ነው ሲሉ ኢትዮጵያዊው የፖለቲካ ሳይንስ ተመራማሪ ተናገሩ - Sputnik አፍሪካ, 1920, 17.05.2025
ሰብስክራይብ

ሩሲያ እና ዩክሬን በኢስታንቡል ለድርድር መቀመጣቸው ለዓለም ሰላም መልካም ተስፋ ነው ሲሉ ኢትዮጵያዊው የፖለቲካ ሳይንስ ተመራማሪ ተናገሩ

ድርድሩ ጥሩ የሰላም ጅምር ነው ሲሉ በኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ኢኒስቲትዩት የጥናትና ምርምር መሪ የሆኑት ዳርእስከዳር ታዬ ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል። አክለውም ዘላቂ ሰላም የግጭቱን ዋና መንስዔዎች መፍታት እንደሚሻ ጠቁመዋል።

"ለሩሲያውያን የግጭቱ ዋና መንስዔ የኔቶ ወደ ምስራቅ አውሮፓ መስፋፋት ነው። ሌላው ደግሞ ዩክሬን ሩሲያኛ ተናጋሪዎች ላይ የምታደርሰው በደል ነው" ብለዋል።

ተመራማሪው አውሮፓውያን ግጭቱ እየሄደ ባለበት መንገድ ደስተኛ እንዳልሆኑ፣ ዩክሬን እንድታሸንፍ እና ሩሲያን ድል ማድረግ እንደሚፈልጉ ገልፀው፤ ይህ የማይሆን ነው ብለዋል።

በአውሮፓውያን እና በአሜሪካውያን መካከል የተፈጠረው ወቅታዊ ልዩነት አሜሪካ ሰላምን እንድትመርጥ፤ አውሮፓ ግን ግጭቱ ይቀጥል የሚል አቋም እንድትይዝ ያደረገ ይመስላልም ብለዋል።

ይህ ክፍፍል መቀጠሉ ላይ ጥሪጣሪያቸውን የገለፁት ተመራማሪው፤ አውሮፓውያን ተቀበሉትም አልተቀበሉትም ሩሲያ እና ዩክሬን ስምምነት ላይ ይደርሳሉ ብለው ተስፋ እንደሚያደርጉ ተናግረዋል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0