የሩሲያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሰርጌ ላቭሮቭ ከአሜሪካ አቻቸው ጋር ኢስታንቡል በተካሄደው ድርድር ዙሪያ በስልክ ተወያዩ
16:10 17.05.2025 (የተሻሻለ: 16:34 17.05.2025)
© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱየሩሲያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሰርጌ ላቭሮቭ ከአሜሪካ አቻቸው ጋር ኢስታንቡል በተካሄደው ድርድር ዙሪያ በስልክ ተወያዩ

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
የሩሲያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሰርጌ ላቭሮቭ ከአሜሪካ አቻቸው ጋር ኢስታንቡል በተካሄደው ድርድር ዙሪያ በስልክ ተወያዩ
ማርኮ ሩቢዮ የዩክሬንን ግጭት ለመፍታት የሚደረገውን ጥረት ለመቀጠል ዋሽንግተን ዝግጁ እንደሆነች አረጋግጠዋል ሲል የሩሲያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታውቋል።
በተጨማሪም የጦር እስረኞችን መለዋወጥ እና የተኩስ አቁም ስምምነት ላይ ለመድረስ አስፈላጊ የሆኑ ቅድመ ሁኔታዎችን ማዘጋጀት ላይ የተደረጉ ስምምነቶችን በበጎው እንደሚቀበሉ ገልፀዋል።
ሰርጌ ላቭሮቭ ሩሲያ በዩክሬን ጉዳይ ላይ ከአሜሪካ ጋር ተባብራ ለመሥራት ዝግጁ መሆኗን አረጋግጠዋል። በተጨማሪም በሩሲያ እና በዩናይትድ ስቴትስ መካከል ስለሚኖረው ቀጣይ ግንኙነት ሀሳብ ተለዋውጠዋል።
የስልክ ውይይቱ የተካሄደው በአሜሪካ አነሳሽነት ነው
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X