ኢትዮጵያ ለደቡብ ሱዳን ተማሪዎች ትሰጥ የነበረውን የነፃ ትምህርት እድል ከሶስት እጥፍ በላይ አሳደገች
15:23 17.05.2025 (የተሻሻለ: 15:44 17.05.2025)
© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱኢትዮጵያ ለደቡብ ሱዳን ተማሪዎች ትሰጥ የነበረውን የነፃ ትምህርት እድል ከሶስት እጥፍ በላይ አሳደገች

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
ኢትዮጵያ ለደቡብ ሱዳን ተማሪዎች ትሰጥ የነበረውን የነፃ ትምህርት እድል ከሶስት እጥፍ በላይ አሳደገች
ከዚህ ቀደም ለደቡብ ሱዳን የድህረ ምረቃ እና የመጀመሪያ ዲግሪ ተማሪዎች 150 ነፃ የትምህርት ዕድሎችን ትሰጥ ነበር።
ይህን ቁጥር አሁን ወደ 645 ማሳደጓን በደቡብ ሱዳን የኢትዮጵያ አምባሳደር ነቢል ማህዲ ገልፀዋል።
በተጨማሪም የኢትዮጵያ መንግሥት በደቡብ ሱዳን ተማሪዎች ላይ ያለውን የገንዘብ ጫና ለማቃለል ቀደም ሲል ይከፍሉት የነበረውን 150 ዶላር የመኖሪያ ፈቃድ ክፍያ ሸፍኗል።
ይህ የተገለፀው አምባሳደሩ ከደቡብ ሱዳን የከፍተኛ ትምህርት፣ የሳይንስና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር ማዱት ቢያር የል ጋር በተወያዩበት ወቅት እንደነበር የሀገሪቱ ሚዲያ ዘግቧል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X