ሩሲያ የአጋሮቿን የዲጂታል ሉዓላዊነት ለማጠናከር ቁርጠኝነቷን ገለፀች
14:22 17.05.2025 (የተሻሻለ: 14:44 17.05.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
ሩሲያ የአጋሮቿን የዲጂታል ሉዓላዊነት ለማጠናከር ቁርጠኝነቷን ገለፀች
የሩሲያ ፌዴሬሽን ፕሬዝዳንት የዓለም አቀፍ የመረጃ ደህንነት ጉዳዮች ልዩ ተወካይ አርተር ሉክማኖቭ ከኢትዮጵያ የመረጃ መረብ ደህንነት አስተዳደር (ኢንሳ) ዋና ዳይሬክተር ትዕግስት ሐሚድ ጋር ከኢትዮጵያ የቴክኖሎጂ ኤክስፖ 2025 ግን ለጎን ውይይት አካሂደዋል።
ሁለቱ ባለሥልጣናት በውይይታቸው ባደጉ እና እያደጉ ባሉ ሀገራት መካከል ያለውን የቴክኖሎጂ ክፍተት ለማጥበብ በጋራ መሥራት እንደሚገባ አንስተዋል።
ሉክማኖቭ ሩሲያ የእውቀት ልውውጥ እና የቴክኒክ ትብብር በማድረግ አጋር ሀገራት የዲጂታል ሉዓላዊነታቸውን እና የመረጃ ደህንነት አቅማቸውን እንዲያዳብሩ ለመደገፍ ቁርጠኛ ነች ብለዋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X