ፑቲን እና ዘለንስኪ የሁለቱ ሀገራት ተወካዮች ስምምነቶች ላይ ከደረሱ ሊገናኙ ይችላሉ ሲሉ የክሬምሊን ቃል አቀባይ ገለፁ
12:18 17.05.2025 (የተሻሻለ: 12:34 17.05.2025)
© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱፑቲን እና ዘለንስኪ የሁለቱ ሀገራት ተወካዮች ስምምነቶች ላይ ከደረሱ ሊገናኙ ይችላሉ ሲሉ የክሬምሊን ቃል አቀባይ ገለፁ

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
ፑቲን እና ዘለንስኪ የሁለቱ ሀገራት ተወካዮች ስምምነቶች ላይ ከደረሱ ሊገናኙ ይችላሉ ሲሉ የክሬምሊን ቃል አቀባይ ገለፁ
በሩሲያ እና ዩክሬን ልዑካን መካከል ሰነዶችን መፈረም በሚመለከት ለሞስኮ ዋነኛው እና መሠረታዊው ነገር ከዩክሬን በኩል ሰነዱን የሚፈርመው ሰው ማንነት ነው ሲሉ ዲሚትሪ ፔስኮቭ ተናግረዋል።
የፔስኮቭ ጋዜጣዊ መግለጫ ተጨማሪ ነጥቦች፦
🟠 በዩክሬን ሰላም ስምምነት ላይ የሚደረገው ሥራ ይቀጥላል።
🟠 ሩሲያ እና ዩክሬን የተኩስ አቁም የቅድመ ሁኔታቸውን ዝርዝር ለመለዋወጥ ተስማምተዋል፤ ሥራዎች ከወዲሁ ተጀምረዋል።
🟠 ፑቲን እና ትራምፕ በስልክ ለመነጋገር ካሰቡ ክሬምሊን ያሳውቃል።
🟠 በሩሲያ እና በዩክሬን መካከል የሚደረጉ ድርድሮች በዝግ መከናወን አለባቸው።
🟠 በኢስታንቡል ከተደረጉት ንግግሮች በኋላ በሩሲያ እና በዩናይትድ ስቴትስ መሪዎች መካከል ምንም ዓይነት ግንኙነት አልነበረም።
🟠 የሩሲያ እና ዩክሬን ቀጣይ ዙር ድርድርን በተመለከተ አሁን ትኩረቱ ስምምነቶቹን መፈፀም ነው ብለዋል።
🟠 ከዩክሬን ጋር ለሚደረገው ድርድር የሩሲያ ልዑካን ቡድንን መቀየር አጀንዳ አይደለም።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X