ፑቲን እና ዘለንስኪ የሁለቱ ሀገራት ተወካዮች ስምምነቶች ላይ ከደረሱ ሊገናኙ ይችላሉ ሲሉ የክሬምሊን ቃል አቀባይ ገለፁ

© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱፑቲን እና ዘለንስኪ የሁለቱ ሀገራት ተወካዮች ስምምነቶች ላይ ከደረሱ ሊገናኙ ይችላሉ ሲሉ የክሬምሊን ቃል አቀባይ ገለፁ
ፑቲን እና ዘለንስኪ የሁለቱ ሀገራት ተወካዮች ስምምነቶች ላይ ከደረሱ ሊገናኙ ይችላሉ ሲሉ የክሬምሊን ቃል አቀባይ ገለፁ - Sputnik አፍሪካ, 1920, 17.05.2025
ሰብስክራይብ

ፑቲን እና ዘለንስኪ የሁለቱ ሀገራት ተወካዮች ስምምነቶች ላይ ከደረሱ ሊገናኙ ይችላሉ ሲሉ የክሬምሊን ቃል አቀባይ ገለፁ

በሩሲያ እና ዩክሬን ልዑካን መካከል ሰነዶችን መፈረም በሚመለከት ለሞስኮ ዋነኛው እና መሠረታዊው ነገር ከዩክሬን በኩል ሰነዱን የሚፈርመው ሰው ማንነት ነው ሲሉ ዲሚትሪ ፔስኮቭ ተናግረዋል።

የፔስኮቭ ጋዜጣዊ መግለጫ ተጨማሪ ነጥቦች፦

🟠 በዩክሬን ሰላም ስምምነት ላይ የሚደረገው ሥራ ይቀጥላል።

🟠 ሩሲያ እና ዩክሬን የተኩስ አቁም የቅድመ ሁኔታቸውን ዝርዝር ለመለዋወጥ ተስማምተዋል፤ ሥራዎች ከወዲሁ ተጀምረዋል።

🟠 ፑቲን እና ትራምፕ በስልክ ለመነጋገር ካሰቡ ክሬምሊን ያሳውቃል።

🟠 በሩሲያ እና በዩክሬን መካከል የሚደረጉ ድርድሮች በዝግ መከናወን አለባቸው።

🟠 በኢስታንቡል ከተደረጉት ንግግሮች በኋላ በሩሲያ እና በዩናይትድ ስቴትስ መሪዎች መካከል ምንም ዓይነት ግንኙነት አልነበረም።

🟠 የሩሲያ እና ዩክሬን ቀጣይ ዙር ድርድርን በተመለከተ አሁን ትኩረቱ ስምምነቶቹን መፈፀም ነው ብለዋል።

🟠 ከዩክሬን ጋር ለሚደረገው ድርድር የሩሲያ ልዑካን ቡድንን መቀየር አጀንዳ አይደለም።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0