የሩሲያ-ዩክሬን የሰላም ሂደት፡ የእስረኞች ልውውጥ ለማካሄድ ስምምነት ላይ መደረሡ "አዲስ ተስፋ ይሰጣል"
20:26 16.05.2025 (የተሻሻለ: 20:44 16.05.2025)
© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱየሩሲያ-ዩክሬን የሰላም ሂደት፡ የእስረኞች ልውውጥ ለማካሄድ ስምምነት ላይ መደረሡ "አዲስ ተስፋ ይሰጣል"

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
የሩሲያ-ዩክሬን የሰላም ሂደት፡ የእስረኞች ልውውጥ ለማካሄድ ስምምነት ላይ መደረሡ "አዲስ ተስፋ ይሰጣል"
በኢስታንቡል የተደረሠው የጦር እስረኞች ልውውጥ ስምምነት “ጠንካራ እርምጃ” እና “ተስፋ ሰጪ ምልክት ነው” ሲሉ ኢትዮጵያዊው የፖለቲካ ሳይንስ እና የዓለም አቀፍ ግንኙነት ባለሙያ በፍቃዱ ዳባ ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል።
ምሁሩ በቀጥታ የሰላም ድርድሩ አውድ የአፍሪካ ሀገራትን ጨምሮ በሩሲያ እና ዩክሬን ግጭት ገለልተኛ የነበሩቱ "አሸናፊ" እንደሚሆኑ ግምታቸውን አስቀምጠዋል።
ግጭቱ በሰላማዊ መንገድ መፈታቱ ለመላው ዓለም በተለይም የሩሲያ እና ዩክሬን ቀውስ በፈጠረው ዓለም አቀፍ ተፅዕኖ ለተጎዱ የአፍሪካ ሀገራት ጠቃሚ እንደሚሆን ባለሙያው ጠቁመዋል።
በሰው ሰራሽ አስተውሎት የበለፀገ ምስል
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X