ኢትዮጵያ የጂኦ ቱሪዝም ስፍራዎቿን ለማስመዝገብ ጥረት በማድረግ ላይ መሆኗን የቱሪዝም ሚኒስቴር አስታወቀ
18:27 16.05.2025 (የተሻሻለ: 18:44 16.05.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
ኢትዮጵያ የጂኦ ቱሪዝም ስፍራዎቿን ለማስመዝገብ ጥረት በማድረግ ላይ መሆኗን የቱሪዝም ሚኒስቴር አስታወቀ
የቱሪዝም ሚኒስትር ዲኤታ ስለሺ ግርማ ከነባሩ የባህል፣ የታሪክ እና የተፈጥሮ ሀብት ጎን ለጎን በጂኦ ፓርክ ልማት ላይ መሥራት አስፈላጊ መሆኑን ለሀገር ውስጥ መገናኛ ብዙኃን ተናግረዋል።
ኢትዮጵያ በርካታ የመካነ ቅርስ ስፍራዎች አሏት ያሉት ሚኒስትር ደኤታው እነዚህን ቦታዎች ቱሪስቶችን ለመሳብ መጠቀም እንደሚገባ ጠቁመዋል።
ሀገሪቱ ለጂኦ ፓርክነት ብቁ የሆኑትን ስፍራዎች በዓለም አቀፍ ደረጃ ለማስመዝገብ ጥረቷን አጠናክራ እንደምትቀጥልም ገልጸዋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X