የብሪክስ ባንክ፦ ለምዕራቡ ዓለም የፋይናንስ ብዝበዛ 'ፈውስ'
20:52 14.05.2025 (የተሻሻለ: 21:14 14.05.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
የብሪክስ ባንክ፦ ለምዕራቡ ዓለም የፋይናንስ ብዝበዛ 'ፈውስ'
"የብሪክስ ባንክ...ለሰው ልጆች ጥቅም፣ እድሎችን ለመፍጠር፣ አማራጮችን ለማሳየት እና እኩልነት እና ፍትሐዊነትን ለማስፈን የተመሠረተ ባንክ ነው" ሲሉ ናይጄሪያዊው ፕሮፌሰር አቡበከር ሳዲቅ አባ ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል።
ብሪክስ ከአይኤምኤፍ እና ከዓለም ባንክ በተለየ ከትርፍ ይልቅ አጋርነትን፤ ከዕዳ ይልቅ ክብርን ያስቀድማል።
እንደ ፕሮፌሰሩ ገለጻ የአስተዳደር አወቃቀሩም ከምዕራባውያን ተቋማት "ሀሰተኛ፣ ሸንጋይ እና ከዳተኛ ባህሪ” በእጅጉ ተቃራኒ ነው።
በተጨማሪም ብሪክስ የአፍሪካን አስፈላጊነት ቀድሞ መገንዘቡን አወድሰዋል።
"ብሪክስ አፍሪካ ቦታ እንደሚገባት መገንዘቡ በጣም ሚዛናዊና ልክ ነው።"
እንደ ኢትዮጵያ ያሉ ሀገራት ባንኩን ለመቀላቀል ጥረት እያደረጉ መሆኑ ብሪክስ ደቡባዊው ዓለም ሉዓላዊነቱን እንዲያስመልስ፣ የዓለም የፋይናንስ ስርዓትን እንደ አዲስ እንዲቀርፅ እና በቀጣይ ፍትሐዊ ኢኮኖሚን እንዲያረጋግጥ እውነተኛ እድል እየሠጠ እንደሆነ ያሳያል ብለዋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X