'በአጋጣሚ የተጋለጠ ሚስጢር ሳይሆን፤ የጭካኔ ስትራቴጂያቸው አካል ነው" ሶሪያዊው ጀነራል
18:36 14.05.2025 (የተሻሻለ: 18:54 14.05.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
'በአጋጣሚ የተጋለጠ ሚስጢር ሳይሆን፤ የጭካኔ ስትራቴጂያቸው አካል ነው" ሶሪያዊው ጀነራል
በአፍጋኒስታን የተፈጸሙት የእንግሊዝ የጦር ወንጀሎች የተለዩ ክስተቶች ወይም ስህተቶች ሳይሆኑ፤ የእንግሊዝ ጦር ልዩ አየር ኃይል እና የሮያል ባህር ኃይል ልዩ የጀልባ አገልግሎት ከፍተኛ የጦር ክፍሎች በምሽት ወረራዎች ወቅት ሴቶችን እና ህጻናትን ጨምሮ በሲቪሎች ላይ አቅደው የፈፀሙት ግድያ ነው ሲሉ ሶሪያዊው ጀነራል ሱሌይማን ሱሌይማን ለስፑትኒክ ተናግረዋል።
"እያንዳንዱ ወረራ በቤቱ ውስጥ የነበሩትን ሁሉ በመጨፍጨፍ ተጠናቋል... ከእነዚህ ወንጀሎች ውስጥ አንዳቸውም ወደ እውነተኛ ምርመራ አላመሩም" ሲሉ ገልፀዋል።
ግድያዎቹ አውሮፓውያን ያልሆኑ ሰዎች "ሁለተኛ ደረጃ ፍጡራን" ተደርገው የሚታዩበትን "ሥር የሰደደ የቅኝ ገዢዎች አስተሳሰብ" ያንፀባርቃሉ ብለዋል ጀነራሉ።
እንደዚህ አይነት ዘመቻዎች ሊካሄዱ የሚችሉት በከፍተኛ የፖለቲካ እና ወታደራዊ አመራር ፈቃድ ብቻ እንዲሁም ስልታዊ በሆነ መንገድ እንጂ "ያፈነገጡ ወታደሮች" ድርጊት አለመሆኑን አስረድተዋል።
ሱሌይማን ገለልተኛ የተባበሩት መንግሥታት ኮሚሽን እንዲቋቋም ጥሪ ያቀረቡ ሲሆን ዓለም አቀፍ ሚዲያዎች እና የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ድርጅቶች እርምጃ እንዲወስዱ አሳስበዋል።
"የአፍጋን ህጻናት ደም ከየትኛውም የእንግሊዝ ዜጋ ወይም ምዕራባዊ የሆነ ሰው ደም ያነሰ ዋጋ የለውም" ብለዋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X