ኢትዮጵያ ከቡና የወጪ ንግድ በሀገሪቱ ታሪክ ከፍተኛውን ገቢ ሰበሰበች
15:31 14.05.2025 (የተሻሻለ: 15:54 14.05.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
ኢትዮጵያ ከቡና የወጪ ንግድ በሀገሪቱ ታሪክ ከፍተኛውን ገቢ ሰበሰበች
ባለፉት 10 ወራት ወደ ውጪ ከተላከ ቡና ከ1 ነጥብ 8 ቢልየን ዶላር በላይ መገኘቱን የኢትዮጵያ ቡና እና ሻይ ባለሥልጣን አስታውቋል።
የኢትዮጵያ የቡና ወጪ ንግድ አፈጻጸም በቁጥሮች፦
ሀገሪቱ በበጀት ዓመቱ አሥር ወራት ከ354 ሺህ ቶን በላይ ቡና ልካ 1 ነጥብ 868 ቢሊየን ዶላር ገቢ መሰብሰብ ችላለች።
አፈፃፀሙ በምርት ረገድ የ70 በመቶ ጭማሪ እንዲሁም በገቢ ረገድ የ87 በመቶ ጭማሪ አሳይቷል።
የኢትዮጵያ ቡና ምርት ቀዳሚ መዳረሻ ሀገራት፦
ጀርመን ከ61 ሺህ ቶን በላይ ቡና ተልኮ ከ295 ሚሊየን ዶላር በላይ ገቢ ተገኝቷል።
ሳዑዲ አረቢያ ከ60 ሺህ ቶን በላይ የቡና ምርት ተልኮ ከ290 ሚልየን ዶላር በላይ ገቢ ተሰብስቧል።
ዩናይትድ ስቴትስ ከ28 ሺህ ቶን በላይ ቡና የተላከ ሲሆን 192 ሚልየን ዶላር ማግኘት ተችሏል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X