ኢትዮጵያ የአፍሪካ የፋይናንስ ኮርፖሬሽን ማቋቋሚያ ስምምነትን ማጽደቋ ተወደሰ
12:24 14.05.2025 (የተሻሻለ: 12:44 14.05.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
ኢትዮጵያ የአፍሪካ የፋይናንስ ኮርፖሬሽን ማቋቋሚያ ስምምነትን ማጽደቋ ተወደሰ
በትናንትናው እለት በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የጸደቀው ስምምነት ሀገሪቱ እያከናወነች ላለው ዘርፈ ብዙ ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ ጉልህ አስተዋጽኦ እንደሚኖረው ተገልጿል።
የስምምነቱን መጽደቅ ተከትሎ የተለያዩ ኢንቨስተሮች ድጋፋቸውን አሰምተዋል፡፡
ኢትዮጵያ በመሠረተ ልማት ኢንቨስትመንቶች ላይ በንቃት በሚሳተፍው አበዳሪ ድርጅት ውስጥ መቀላቀሏ በፕሮጀክቶች ላይ የሚያጋጥሙ ማነቆዎችን ለመቀረፍ እና የኢኮኖሚ ማሻሻያ አጀንዳዎቿን ለመደገፍ የሚያስችላት ነው ተብሏል፡፡
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X