የኢትዮጵያ የኢኮኖሚ ማሻሻያ ከህንድ ጋር ያላትን የንግድ እና የኢንቨስትመንት ግንኙነት በከፍተኛ ደረጃ ማሳደጉ ተነገረ
11:35 13.05.2025 (የተሻሻለ: 11:54 13.05.2025)
© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱየኢትዮጵያ የኢኮኖሚ ማሻሻያ ከህንድ ጋር ያላትን የንግድ እና የኢንቨስትመንት ግንኙነት በከፍተኛ ደረጃ ማሳደጉ ተነገረ

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
የኢትዮጵያ የኢኮኖሚ ማሻሻያ ከህንድ ጋር ያላትን የንግድ እና የኢንቨስትመንት ግንኙነት በከፍተኛ ደረጃ ማሳደጉ ተነገረ
የህንድ ጠቅላይ ሚኒስትር ፅህፈት ቤት ሚኒስትር ዳኤታ ጂቴንድራ ሲንግ በተለይም ሀገራቸው በማኑፋክቸሪንግ፣ በግብርና፣ በመሠረተ ልማት እና በአይሲቲ ዘርፎች ኢትዮጵያ ውስጥ ከፍተኛ የመዋዕለ ነዋይ ፈሰስ እያደረገች እንደሆነ ተናግረዋል።
ባለሥልጣኑ ይህን ያሉት በህንድ ጉብኝት ላይ ከሚገኘው ከፍተኛ የኢትዮጵያ ልዑካን ጋር ውይይት ባደረጉበት ወቅት እንደሆነ የሀገሪቱ መገናኛ ብዙኃን ዘግቧል።
አክለውም ከ650 በላይ የህንድ ኩባንያዎች በኢትዮጵያ ኢንቨስት እያደረጉ እንደሆነና በአጠቃላይ ከ5 ቢሊዮን ዶላር በላይ ካፒታል በማስመዝገብ በኢትዮጵያ ሁለተኛ የውጭ ቀጣሪዎች መሆናቸውን ጠቁመዋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X